Blue Board
Blue Board is an Ai service platform, where every workflow is automated. We transform complex, manual processes in to streamlined, self-running systems.
ኤርምያስ ምዕራፍ40፥ ከቁጥር 35 -38
02/05/2026
Ethiopian economy insights to come soon.
The Infliction Point is here.
የአማራ ባንክ በ2018 መጀመሪያ አምስት ወራት 1.15 ቢሊዮን ብር ትርፍ አስመዘገበ።
አዲስ አበባ፣ ኢትዮጵያ፣ ታህሳስ 03 ቀን 2018 ዓ.ም የአማራ ባንክ በ2018 በጀት ዓመት የመጀመሪያዎቹ አምስት ወራት ብቻ (ከሐምሌ 1 እስከ ህዳር 30 ቀን 2018) በዋና ዋና የፋይናንስ አፈጻጸም ቁልፍ የሥራ መስኮች ላይ ጠንካራና ከፍተኛ ዕድገት በማስመዝገብ ከታክስ በፊት የ1.15 ቢሊዮን ብር ትርፍ አስመዝግቧል።
ይህ የላቀ ትርፍ የተገኘው በ2017 በጀት ዓመት ከተመዘገበው የ910.2 ሚሊዮን ብር ኪሳራ ጋር ሲነፃፀር ከፍተኛ መሻሻል አሳይቷል። በበጀት ዓመቱ የመጀመሪያ አምስት ወራት 3.55 ቢሊዮን ብር ገቢ ማስመዝገብ እንደተቻለ ዋና ስራ አስፈፃመሚው ጠቅሰዋል።
ዋና ሥራ አስፈፃሚው አክለውም በእነዚህ አምስት ወራት ውስጥ የተመዘገበው አፈጻጸም ስትራቴጂካዊ ትኩረት በጠንካራ የሀብት ማሰባሰብ፣ በዲጅታል ትራንስፎርሜሽንና በብድር አስተዳደር ላይ ጥንቃቄ በተሞላበት ሁኔታ ላይ አተኩሮ መስራት በመቻላቸው የመጣ ነው ብለዋል።
ቁልፍ የአፈጻጸም ዋና ዋና መረጃዎች፡-
የተቀማጭ ገንዘብ አሰባሰብ፡
አጠቃላይ የተቀማጭ ገንዘብ መጠን እስከ ህዳር 2018 ዓ.ም 35.8 ቢሊዮን ብር የደረሰ ሲሆን፣ ዕድገቱ 82 በመቶ ሆኗል። ይህም በአምስት ወራት ጊዜ ውስጥ የ4.29 ቢሊዮን ብር ብልጫ አሳይቷል።
የውጭ ምንዛሪ (FCY) አሰባሰብ፡-
የአማራ ባንክ የ76.58 ሚሊዮን የአሜሪካን ዶላር ገቢ በመሰብሰብ የላቀ አፈጻጸም አሳይቷል፣ ይህም ካለፈው ዓመት ተመሳሳይ ወቅት ጋር ሲነጻጸር የ313 በመቶ ብልጫ አለው።
የብድር አቅርቦትና የሀብት ጥራት፡-
አማራ ባንክ ከተመሰረተ ጀምሮ ያቀረበው አጠቃላይ ብድርና የቅድሚያ ክፍያ አምና በተመሳሳይ ወቅት ከነበረበት በ53.8 በመቶ በማሳደግ ወደ 31.3 ቢሊዮን ብር አበድሯል።
በብድር አሰባሰብ፡-
በህዳር 2017 ከነበረበት 12.9 በመቶ በከፍተኛ ሁኔታ በመቀነስ ያልተከፈለ/የተበላሸ/ ብድር (NPL) ጥምርታ በአስደናቂ ሁኔታ በማውረድ ወደ 4.06 በመቶ እንዲደርስ ርብርብ ተደርጓል።
ከዚህ ጋር በተያያዘ ኅዳር 20 ቀን 2018 ዓ.ም ተካሂዶ በነበረው በባንኩ 4ኛ ዓመታዊ የባለአክሲዮኖች ጉባኤ ላይ በከፍተኛ ጉጉት የተሰባሰበው ተሳታፊ ከጠዋቱ ጀምሮ ሲታይ አስደሳች ድባብ ፈጥሮ የነበረ ሲሆን በአስደናቂው ቀን ከጠዋቱ 3፡30 ላይ ዝቅተኛው የምልአተ ጉባኤ ገደብ መሟላት ብቻ ሳይሆን በከፍተኛ ደረጃ መሻገር ችሎ ነበር። ይህም ባለአክሲዮኖች በአማራ ባንክ ራዕይ እና አመራር ላይ ያላቸውን ጥልቅ እምነትና ቁርጠኝነት ያሳያል።
ለዚህምልባዊ ምስጋናችንን እናቀርባለን።
አማራ ባንክ
ከባንክ ባሻገር!
አማራ ባንክ!
ፕሮጀክቱ 2017/18 GC ከተፀነሰበት ጀምሮ እስከዛሬ ድረስ ውስጣዊና ውጫዊ ጫና ተቋቁሞ የሚገኝ ጠንካራና ጀማሪ ተቋም አማራ ባንክ ነው።
ፕሮጀክቱ የተጀመረውና ዕውን የሆነው በተቋም ግንባታ ልምድ፥ የትምህርት ዝግጅት እና ቅንነቱ ባላቸው፥ በሚዲያ የማይታወቁ ሃቀኛ ሙሁራን እና በ190ሽ ባለአክሲዮኖች ቁርጠኛነት ነው።
በተቃራኒው፦
1) ከፕሮጀክቱ ወቅት ጀምሮ በሚዲያ ሱስ የሰከሩ፥ የሙያ ስነምግባርና የቢዝነስ አቅል (Business Acumen) የሌላቸው አባላት ባንኩ ሲመሰረትም እንቅፋት ሆነው የቆዩ ግለሰቦች በአይነትና በፍላጎት በርካቶች ናቸው።
እነዚያ የፕሮጀክቱን እንቅስቃሴ እየተከታተሉ፥ በየፌቡ ገፁ ሲያሰጡ፥ የቆዩ ዛሬም እራሳቸውን የባንኩ ፈጣሪና ወላጅ አባት እንደሆኑ ቆጥረው መስዋዕትነት የከፈሉ የፕሮጀክቱን ሃላፊዎች፥ የቴክኒክ አባላት እና የ190ሽ ባለድርሻ አባላት ሚና ማሳነስ ተገቢ አይደለምና ከድርጊታችሁ ታቀቡ በሏቸው።
2) በጎጥና ጥቅም ሰንሰለት አንገታችሁ የተሳሰረ ግለሰቦች ዛሬም "አማራ ባንክ ፈረሰ" ብላችሁ "ቂቤ ጠጣን" የምትሉ፥ የህልም ቂቤ ጠጥታችሁ ይሆናል እንጅ፥ በዕውን አባ አልፈረሰም፤ ይልቁንስ ለባንኩ ስኬት ያላችሁን አሳፋሪ ግላዊ ስሜት(ego) ያሳያልና፥ ከዚህ ስንኩል አስተሳሰባችሁ በመታቀብ ለተቋማት ስኬት የሚሆን የዝምታ አስተዋፅኦ ብታበረክቱ የተሻለ ነው።
አስተዳደራዊ ዕርምቶች፦
3) አማራ ባንክ እንደ ተቋም፥
ተልዕኮ ተቀብለው የባንኩን የዕለት ከዕለት እንቅስቃሴ ሚስጥርና ሰነድ በሚያባክኑ (ነባርና የበፊት ሰራተኞች)፥ ክትትል በማድረግ አስተዳደራዊ ዕርምት ሊያደርግ ይገባል።
4)ባንኩን የራሳቸው አድርገው እንዲጠብቁት፥ የተመሰረተበትን አላማ፥ተልዕኮና ራዕይ ከግብ እንዲያደርስ፥ ሰራተኞችን የተለያዩ ማበረታቻ ፕሮግራሞችን በመዘርጋት ማነቃቃት ተገቢ እንደሆነ አምናለሁ።
በቅርቡ የተጀመረው የደመወዝ ጭማሪ በተመለከተ የተደረገው ውይይት ተፈፃሚ እንደሚሆን እምነቴ ነው።
ባለአክሲዮኖች፥
አማራ ባንክ በታሪክ ሪከርድ የሰበረ፥ ከፍተኛ ቁጥር የተሳተፈበት የባለድርሻ አካላት ተቋም እንደመሆኑ መጠን፥ ለበለጠ ስኬት የኛ የባለአክስዮኖች ብርቱ ፅናትና ትግስት ወሳኝ መሆኑን አውቀን ባንካችንን እንጠበቅ ።
ከአክብሮት ጋር!
07/01/2025
Start Now Take control of your future with Coursiv. Learn AI-powered strategies to thrive in online business, freelance, and beyond.
06/05/2025
Detention MDs for Requesting Pay Raise is Totally Unjust.
HAPPY EASTER
Click here to claim your Sponsored Listing.
Contact the public figure
Telephone
Website
Address
Dallas, TX
Opening Hours
| Monday | 8am - 6pm |
| Tuesday | 9am - 5pm |
| Wednesday | 8am - 6pm |
| Thursday | 8am - 6pm |
| Friday | 8am - 6pm |
| Saturday | 8am - 6pm |
| Sunday | 9am - 1pm |
02/27/2024