Labena's library
for learn each other
12/03/2025
የኢትዮጵያ ወንጌል አማኞች አብያተክርስቲያናት ካውንሰል መገለጫ ሰጠ።
ከቅርብ ዓመታት ጀምሮ ወደ ምድራችን የሚመጡ የንስሐ ግቡ ሐልዕክቶች ሰለሆኑ ባላፈው ዓመት ታላቅ የአገራዊ ንስሃ ጊዜን በአደባባይ አከናውነናል። ይህንን ንስሃ መቀጠል ስለታመነበት የአገራዊ ንስሃ የሚያስተባብር ግብረ ኃይል በወንጌል አማኞች አብያተክርስቲያናት ካውንስል ይሁንታ ተቋቁሞ ተግባሮቹን በተሻለ መንገድ ለመወጣት በመሥራት ላይ ይገኛል።
ስለዚህ ፦
1.ከሚያዝያ 6 እስከ 11/2017 ዓ.ም ከሰኞ- ቅዳሜ በሉት የህማማቱ ሳምንት በመላው አገሪቱ ባሉ ማህበር ምዕመናን ቢቻልም በከተሞች አመቺ በሆኑ በተመረጡ አብያተክርስቲያናት በአንድነት በመሰባሰብ የኑዛዜና የንስሐ ቀናቶች እንዲሆኑ።
2. ከሚያዝያ 19 እስከ ግንቦት 17/2017 ዓ.ም ባሉት ሳምንታት ኑዛዜ ያደረግንባቸው ጉዳዮችን ወደ ፍሬ እንዲመጡ በየአጥቢያው የንስሐ አቅጣጫዎች የትምህርት እና ንስሃውን ከሕይወት ጋር የምሰናዛምድባቸው ጊዜያቶች እንዲሆኑ።
3.ግንቦት 24 ቀን 2017ዓ.ም በሁሉም ከተሞችና አካባቢዎች የማጠቃለያ የንሰሐ ጊዜ መሪዎች በየክልሎቻቸው የካውንስል እና የኀብረቶች አደረጃጀቶች እንዲያደርጉና በአዲስ አበባ ለሚካሄደው ለአገር አቀፉ የማጠቃለያ የንስሐ ጊዜ ከልሉን የሚወክሉ መሪዎችን ወክለውና በክልሉ ቤተክርስቲያን መለኮታዊ ሥልጣን ጸልየውላቸው ወደ አዲስ አበባ እንዲልኩ።
4.ከግንቦት 25 አስከ 27 2017 ዓ.ም ለሦስት ቀናት ከመላው ኢትዮጵያ ክልሎች እና ከዲያስፖራ በክልሎች ቤተክርስቲያን መለኮታዊ ሰልጣን በሚወከሉ መሪዎች በአዲስ አበባ ከተማ ማጠቃለያውን በተወከሉ መሪዎች የንስሐ ጊዜ በማድረግ የንሰሐ ማጠቃለያ እንዲሆን ታቅዷል።
በመላው ኢትዮጵያ እና በውጭ ሀገር የምትኖሩ የወንጌላውያን አማኞች ሁሉ በዚህ በወጣው ፕሮግራም መስረት አሰተባባሪ ግብር ኃይል በልዩ ልዩ መገናኛ ዘዴዎች በሚያሰራጫቸው የንስሐ አቅጣጫዎች እና የኑዛዜ የጸሎት ርዕሶች አየታገዛቸሁ የንስሐ ጊዜውን አብረን በጋራ እንድናከናውን ጥሪዬን አቀርባለሁ።
“ኢየሩሳሌም ሆይ፥ ጕበኞችን በቅጥርሽ ላይ አቁሜአለሁ፤ ቀንና ሌሊት ከቶ ዝም አይሉም፤ እናንተ እግዚአብሔርን የምታሳስቡ፥ ኢየሩሳሌምን እስኪያጸና በምድርም ላይ ምስጋና እስኪያደርጋት ድረስ አትረፉ ለእርሱም ዕረፍት አትስጡ።”ትንቢተ ኢሳይያስ 62፥6-7
ልዑል አግዚአብሔር አገራችንን ኢትዮጵያን ይባርክ!!
የኢትዮጵያ ወንጌል አማኞች አብያተ ከርስቲያናት ካውንስል ጠቅላይ ጸሐፊ ቁስ ደረጀ ጀምበሩ
11/03/2025
11/03/2025
11/03/2025
Matthew 7:12 So in everything, do to others what you would have them do to you, for this sums up the Law and the Prophets. | New International Version (NIV) | Download The Bible App Now So in everything, do to others what you would have them do to you, for this sums up the Law and the Prophets.
11/03/2025
ዕብራውያን 12
¯¯¯¯¯¯¯¯¯¯
¹-² እንግዲህ እነዚህን የሚያህሉ ምስክሮች እንደ ደመና በዙሪያችን ካሉልን፥ እኛ ደግሞ ሸክምን ሁሉ ቶሎም የሚከበንን ኃጢአት አስወግደን፥ የእምነታችንንም ራስና ፈጻሚውን ኢየሱስን ተመልክተን፥ በፊታችን ያለውን ሩጫ በትዕግሥት እንሩጥ፤ እርሱ ነውርን ንቆ በፊቱም ስላለው ደስታ በመስቀል ታግሦ በእግዚአብሔር ዙፋን ቀኝ ተቀምጦአልና።
³ በነፍሳችሁ ዝላችሁ እንዳትደክሙ፥ ከኃጢአተኞች በደረሰበት እንዲህ ባለ መቃወም የጸናውን አስቡ።
⁴ ከኃጢአት ጋር እየተጋደላችሁ ገና ደምን እስከ ማፍሰስ ድረስ አልተቃወማችሁም፤
⁵-⁶ እንደ ልጆችም ከእናንተ ጋር፦ ልጄ ሆይ፥ የጌታን ቅጣት አታቅልል፥ በሚገሥጽህም ጊዜ አትድከም፤ ጌታ የሚወደውን ይቀጣዋልና፥ የሚቀበለውንም ልጅ ሁሉ ይገርፈዋል ብሎ የሚነጋገረውን ምክር ረስታችኋል።
⁷ ለመቀጣት ታገሡ፤ እግዚአብሔር እንደ ልጆች ያደርግላችኋልና፤ አባቱ የማይቀጣው ልጅ ማን ነው?
⁸ ነገር ግን ሁሉ የቅጣት ተካፋይ ሆኖአልና ያለ ቅጣት ብትኖሩ ዲቃላዎች እንጂ ልጆች አይደላችሁም።
⁹ ከዚህም በላይ የቀጡን የሥጋችን አባቶች ነበሩን እናፍራቸውም ነበር፤ እንዴትስ ይልቅ ለመናፍስት አባት አብልጠን ልንገዛና በሕይወት ልንኖር በተገባን?
¹⁰ እነርሱ መልካም ሆኖ እንደ ታያቸው ለጥቂት ቀን ይቀጡን ነበርና፥ እርሱ ግን ከቅድስናው እንድንካፈል ለጥቅማችን ይቀጣናል።
¹¹ ቅጣት ሁሉ ለጊዜው የሚያሳዝን እንጂ ደስ የሚያሰኝ አይመስልም፥ ዳሩ ግን በኋላ ለለመዱት የሰላምን ፍሬ እርሱም ጽድቅን ያፈራላቸዋል።
¹² ስለዚህ የላሉትን እጆች የሰለሉትንም ጉልበቶች አቅኑ፤
¹³ ያነከሰውም እንዲፈወስ እንጂ እንዳይናጋ፥ ለእግራችሁ ቅን መንገድ አድርጉ።
¹⁴ ከሰው ሁሉ ጋር ሰላምን ተከታተሉ ትቀደሱም ዘንድ ፈልጉ፥ ያለ እርሱ ጌታን ሊያይ የሚችል የለምና።
¹⁵ የእግዚአብሔር ጸጋ ለማንም እንዳይጎድለው፥ ብዙዎቹም የሚረክሱበት አንድ መራራ ሥር ወደ ላይ በቅሎ እንዳያስጨንቅ፥ ሴሰኛም የሚሆን እንዳይገኝ፥
¹⁶ ወይም ስለ አንድ መብል በኵርነቱን እንደ ሸጠ እንደ ዔሳው ለዚህ ዓለም የሚመች ሰው እንዳይሆን ተጠንቀቁ።
¹⁷ ከዚያ በኋላ እንኳ በረከቱን ሊወርስ በወደደ ጊዜ እንደ ተጣለ ታውቃላችሁና፤ በእንባ ተግቶ ምንም ቢፈልገው ለንስሐ ስፍራ አላገኘምና።
04/03/2025
የኢትዮጵያ የባሕር በር ጥያቄ ለየትኛውም የጎረቤት ሀገር ስጋት ሊሆን አይገባም
**********************
(ኢ ፕ ድ)
የተለያዩ ሀገራት ከርቀት በመምጣት በቀይ ባሕር የጦር ሰፈር ማቋቋም ደረጃ እየደረሱ ባሉበት ሁኔታ ኢትዮጵያ ከተቀረው ዓለም ጋር መገናኘት እንድትችል የባህር በር መጠየቋ ስጋት የሚሆንበት ምክንያት እንደሌለ በአዲስ አበባ ዩኒቨርሲቲ መምህር ፕሮፌሰር አድማሱ ገበየሁ ተናገሩ።
ኢትዮጵያ ስትጠይቅ በነጻ ስጡኝ አላለችም፤ ጥያቄው የቀረበው በሰጥቶ መቀበል መርህን ነው ብለዋል።
እፕሮፌሰር አድማሱ ገበየሁ ለኢፕድ እንደገለፁት ኢትዮጵያ በአፍሪካ ቀንድ ትልቋ ሀገር መሆኗን ብዙዎቹ የዓለም ሀገራት ይቀበላሉ፡፡ ኢትዮጵያ ባላት ሀገራዊ ሀብትና በሕዝብ ብዛት አሁን ባለው ወቅታዊ መረጃ ትልቅ ሀገር ናት፡፡
ኢትዮጵያ የባሕር በር አግኝታ ይበልጥ ተጠቃሚ ብትሆን ጎረቤት ሀገራትን ጨምሮ ሌሎችም ገበያቸው ይሰፋል፤ ተጠቃሚ ይሆናሉ እንጂ ሊገጥማቸው የሚችል ችግር አይኖርም ያሉት ፕሮፌሰር አድማሱ፤ አንዳንድ ሀገራትና ግለሰቦች የባሕር ኃይል መቋቋሙን እንደ ስጋት ሲመለከቱ እናያለን። ይህ ግን ስህተት ነው ብለዋል።
ሀገሪቷ ወደብ ላይ የሚንቀሳቀስ ሀብትና ንብረት አላት፡፡ በአካባቢው የሚንቀሳቀሱ የባሕር ላይ ወንበዴዎች አሉ፡፡ ሀብት ንብረቷን በመጠበቅ ራሷን ከእነዚህ ኃይሎች ለመከላከል የሰለጠነ ወታደራዊ የባሕር ኃይል ያስፈልጋታል።
ኢትዮጵያ በምንም መልኩ በጉልበቷ ከሌላ ለመንጠቅ የተንቀሳቀሰችበት ታሪክ እንደሌላት አመልክተው፤ የባሕር በር ለማግኘት በቅርብ ጊዜ የሰማነው ከሶማሌ ላንድ ጋር ያለው ጉዳይ ብቻ ሳይሆን ከሌሎችም ዙሪያችን ካሉ የቅርብም ሆነ የሩቅ የባሕር በር ባለቤቶች ጋር በተለያየ ደረጃ ሙከራዎች እየተደረጉ ነው፡፡ ከሁሉም ጎረቤቶቻችን ጋር የባሕር በር በተመለከተ መነጋገርና ሁኔታዎችን የተሻለ የማድረግ ሂደትን መከተሉ ተገቢና ሊቀጥል የሚገባው እንደሆነ ገልጸዋል።
ኢትዮጵያም የተለያዩ ሀገራት ወደ ቀጣናው እየመጡ በቀይ ባሕር ላይ የጦር ሰፈር እየገነቡ ባሉበት ወቅት ከመቶ ኪሎ ሜትር ባነሰ ርቀት ላይ ያለችው ኢትዮጵያ የባሕር በር ጥያቄ ማቅረቧ ላይ ቅሬታ ማሰማት ትርጉም የለውም ብለዋል።
Click here to claim your Sponsored Listing.
Category
Telephone
Website
Address
S**o