Capital
Capital is the longest-established private English newspaper in Ethiopia Capital is the longest established private English newspaper in Ethiopia
03/05/2026
የአፍሪካ ቁጥር አንድ ቢሊየነር አሊኮ ዳንጎቴ የሀብት መጠን በከፍተኛ ሁኔታ ጨመረ
የአፍሪካ ቁጥር አንድ ባለሀብት የሆኑት ናይጄሪያዊው አሊኮ ዳንጎቴ፣ ባለፉት ጥቂት ቀናት ውስጥ ብቻ በሀብታቸው ላይ ከፍተኛ እድገት ማስመዝገባቸው ተሰማ።
እንደ ብሉምበርግ የቢሊየነሮች መረጃ መሠረት፣ የዳንጎቴ ጠቅላላ የሀብት መጠን ወደ 34.0 ቢሊዮን ዶላር ከፍ ብሏል።
ይህ የሀብት ዝላይ በፈረንጆቹ 2026 ዓመት ውስጥ ብቻ 3.99 ቢሊዮን ዶላር ትርፍ እንዲያገኙ ያስቻላቸው ሲሆን፣ በዓለም አቀፍ የሀብታሞች ዝርዝር ውስጥም ወደ 69ኛ ደረጃ ላይ እንዲቀመጡ አድርጓቸዋል።
ምንም እንኳን ሌሎች አፍሪካውያን ቢሊየነሮች በዓመቱ ውስጥ ያስመዘገቡት የትርፍ ዕድገት መጠን ከእሳቸው ቢበልጥም፣ ዳንጎቴ አሁንም የአህጉሪቱን ቀዳሚነት በሰፊ ልዩነት እንደያዙ ቀጥለዋል።
ከዚህ የሀብት እድገት ጋር ተያይዞ በሌጎስ የሚገኘው የናይጄሪያው ዳንጎቴ የነዳጅ ማጣሪያ ለኢትዮጵያ አየር መንገድ የቀጥታ የጄት ነዳጅ አቅርቦት መጀመሩ የተዘገበ ሲሆን፣ ይህም ከአፍሪካ ግዙፍ አየር መንገድ ጋር ያለውን የኢነርጂ ትስስር አጠናክሮታል።
ማጣሪያው በቀን 650,000 በርሜል የማምረት ሙሉ አቅሙን እየተጠቀመ ሲሆን፣ የጄት ነዳጅ ኤክስፖርትም በቀን ወደ 158,000 በርሜል ከፍ ብሏል። በሆርሙዝ የባህር ሰርጥ በተፈጠረው የአቅርቦት መቋረጥ ምክንያት ለነዳጁ ያለው ፍላጎት እየጨመረ መጥቷል።
03/05/2026
አሜሪካ ለመካከለኛው ምስራቅ ሀገራት የ8.6 ቢሊዮን ዶላር የጦር መሳሪያ ሽያጭ አፀደቀች
የፕሬዝዳንት ዶናልድ ትራምፕ አስተዳደር ለታቀዱት የጦር መሳሪያ ሽያጮች የኮንግረሱን ግምገማ በድንገተኛ ሁኔታ በማለፍ፣ ለእስራኤል፣ ለኳታር፣ ለተባበሩት አረብ ኤምሬትስ እና ለኩዌት የሚቀርብ በድምሩ 8.6 ቢሊዮን ዶላር የሚያወጣ የጦር መሳሪያ ጥቅል ማጽደቁ ተገለጸ።
የአሜሪካ የውጭ ጉዳይ ሚኒስትር ማርኮ ሩቢዮ ሽያጩን አስመልክተው በሰጡት መግለጫ፣ ሽያጩ በአስቸኳይ እንዲከናወን የሚያስገድድ "አስቸኳይ ሁኔታ" መፈጠሩን ገልጸዋል።
ይህ ውሳኔ የተላለፈው አሜሪካና እስራኤል በኢራን ላይ የጀመሩት ጦርነት ዘጠነኛ ሳምንቱን በያዘበትና በ ቀጠናው ያለው ውጥረት በጨመረበት ወቅት ነው።
ይህ የአሜሪካ እርምጃ የመጣው ኢራን በአጎራባች ሀገራት ላይ የአየር ጥቃት መፈጸሟን ተከትሎ ሲሆን፣ በሌላ በኩል በአሜሪካ እና በኔቶ አጋሮች መካከል ያለው ልዩነት እየሰፋ መሄዱ ተስተውሏል።
ትራምፕ በጀርመኑ መራሄ መንግስት ፍሬድሪክ ሜርዝ ላይ በሰነዘሩት ትችት ሳቢያ፣ አሜሪካ በጀርመን የሚገኘውን የሰራዊት ቁጥር ለመቀነስ መወሰኗ ውጥረቱን አባብሶታል።
የጀርመን መከላከያ ሚኒስትር ቦሪስ ፒስቶሪየስ በሰጡት ምላሽ፣ የአሜሪካ ውሳኔ የሚጠበቅ መሆኑን ገልጸው፣ "እኛ አውሮፓውያን ለራሳችን ደህንነት የበለጠ ኃላፊነት መውሰድ ይኖርብናል" ብለዋል።
የአሜሪካ የውጭ ጉዳይ መሥሪያ ቤት ይህ የተፋጠነ የጦር መሳሪያ ዝውውር "ለአሜሪካ ብሔራዊ ደህንነት ጥቅም ሲባል" የተደረገ መሆኑን አጽንኦት ሰጥቷል። በአሁኑ ወቅት በአሜሪካ እና በኢራን መካከል ያለው ጦርነት በአሜሪካ ላይ ብቻ 25 ቢሊዮን ዶላር ወጪ ማስከተሉን የፔንታጎን መረጃዎች ያመለክታሉ።
03/05/2026
የንግድ ባንክ የሀብት መጠን 2.87 ትሪሊዮን ብር መድረሱ ተገለጸ
የኢትዮጵያ ንግድ ባንክ የ2018 በጀት ዓመት የዘጠኝ ወራት የሥራ አፈጻጸሙን በገመገመበት ወቅት፣ የባንኩ አጠቃላይ የሀብት መጠን 2.87 ትሪሊዮን ብር መድረሱን አስታውቋል።
የባንኩ ፕሬዚዳንት አቶ አቤ ሳኖ እንደገለጹት፣ ባንኩ በነዚህ ወራት ውስጥ 54.5 ቢሊዮን ብር ያልተጣራ ትርፍ ማስመዝገብ ችሏል።
ከሀብት እድገቱ በተጨማሪ፣ ባንኩ ለተለያዩ የኢኮኖሚ ዘርፎች 514.6 ቢሊዮን ብር ብድር ያቀረበ ሲሆን፣ ከዚህ ውስጥ ከፍተኛው ድርሻ (471.9 ቢሊዮን ብር) ለግሉ ዘርፍ የቀረበ መሆኑ ተገልጿል።
ይህ የብድር አቅርቦት ከዕቅድ በላይ 106 በመቶ አፈጻጸም የታየበት መሆኑንም የስትራቴጂክ ዕቅድና ትራንስፎርሜሽን ምክትል ፕሬዚዳንት አቶ ወጋየሁ ገብረማርያም በሪፖርታቸው አመልክተዋል።
ባንኩ ዲጂታል ባንኪንግን በማስፋፋት ረገድም ውጤታማ ስራዎችን ማከናወኑን የገለጹት ፕሬዚዳንቱ፣ ከ814 ሺህ በላይ አዳዲስ የዲጂታል ተበዳሪዎችን ማፍራት መቻሉም ተጠቁሟል።
02/05/2026
የአፍሪካ ነጻ ንግድ ቀጠናን ውጤታማ ለማድረግ የፖሊሲ ማሻሻያዎች እና የመሰረተ ልማት ዝርጋታ እንዲጠናከሩ ተጠየቀ
የአፍሪካ አህጉራዊ ነጻ ንግድ ቀጠና (AfCFTA) ስምምነትን በኢትዮጵያ ውጤታማ በሆነ መንገድ ተግባራዊ ለማድረግ የፖሊሲ ማሻሻያዎች፣ ጠንካራ የመሰረተ ልማት ዝርጋታ እና የመንግስታት ቁርጠኝነት ወሳኝ መሆናቸውን የአዲስ አበባ ንግድና ዘርፍ ማህበራት ምክር ቤት (አዲስ ቻምበር) አሳሰበ።
ምክር ቤቱ ከኤክስፐርቲዝ ፍራንስ እና ከኤኮ ትሬድ ፕሮጀክት ጋር በመተባበር ባዘጋጀው የፓናል ውይይት ላይ እንደተገለጸው፤ የነጻ ንግድ ቀጠናው በዓለም ደረጃ ግዙፍ የገበያ ዕድል ይዞ የመጣ ቢሆንም፣ ኢትዮጵያውያን ኩባንያዎች በተለይም አነስተኛና መካከለኛ የንግድ ተቋማት ከዚህ ዕድል ተጠቃሚ እንዲሆኑ መሰረታዊ ማሻሻያዎች ያስፈልጋሉ።
የአዲስ ቻምበር ምክትል ዋና ፀሐፊ አቶ ካሳሁን ማሞ በውይይቱ ላይ እንደገለጹት፣ የአፍሪካ ስነ-ህዝብ በ2050 ወደ 2.5 ቢሊዮን ያድጋል ተብሎ የሚጠበቅ ሲሆን፣ ይህም ለሀገር ውስጥ ኩባንያዎች ሰፊ የገበያ አድማስ ይከፍታል።
ሆኖም ይህንን ዕድል ለመጠቀም በኩባንያዎች ደረጃ የሚታዩ የአደረጃጀትና የሰው ኃይል ችግሮች መፈታት እንዳለባቸው ጠቁመዋል።
በተጨማሪም የነጻ ንግድ ቀጠናውን ውጤታማ ለማድረግ የፋይናንስና የኢኮኖሚ ተቋማትን አሠራር ማሻሻል፣ የኢንቨስትመንት ፖሊሲዎችን በየጊዜው መቃኘትና የዲጂታል ቴክኖሎጂ ዕውቀትን ማጠናከር፣ የሎጀስቲክስ እና የመሠረተ ልማት አውታሮችን በስፋት መዘርጋት እንዲሁም የንግድ ድጋፍ አገልግሎቶችንና የግንዛቤ ማስፋፊያ ሥራዎችን ማከናወን እንደሚገባ ምክረ-ሐሳቦች ቀርበዋል።
02/05/2026
አሜሪካ በጣለችው የባህር ላይ እገዳ ሳቢያ ኢራን 4.8 ቢሊዮን ዶላር አጣች
በአሜሪካው ፕሬዝዳንት ዶናልድ ትራምፕ ትዕዛዝ በኦማን ባህረ ሰላጤ ላይ የተጣለው የባህር ላይ እገዳ፣ ኢራን በሦስት ሳምንታት ውስጥ ብቻ 4.8 ቢሊዮን ዶላር የነዳጅ ገቢ እንድታጣ አድርጓታል።
የፔንታጎን ባለስልጣናትን የጠቀሰው የአክሲዮስ ዘገባ እንደሚያመለክተው፣ ካለፈው ሚያዝያ 5 ቀን 2018 ዓ.ም. ጀምሮ ተግባራዊ በሆነው በዚህ እገዳ ምክንያት 53 ሚሊዮን በርሜል ድፍድፍ ነዳጅ የጫኑ 31 ታንከሮች በባህር ላይ ቆመው እንዲቀሩ ተደርገዋል።
እገዳው አሜሪካ በተኩስ አቁም ድርድሮች ላይ እንደ መደራደሪያ ለመጠቀም ባሰበችው ስትራቴጂ የተጣለ ሲሆን፣ እስካሁን ከ40 በላይ መርከቦች መንገዳቸውን እንዲቀይሩ ተገደዋል።
በየብስ ላይ ያሉት የነዳጅ ማከማቻዎች አቅማቸው በመሙላቱ ኢራን ያረጁ መርከቦችን እንደ ተንሳፋፊ ማከማቻ ለመጠቀም ብትገደድም፣ በጥቂት ሳምንታት ውስጥ የማከማቻ ቦታው ሙሉ በሙሉ ካለቀ የነዳጅ ጉድጓዶቿን ለመዝጋት ልትገደድ እንደምትችል ተነግሯል።
አንዳንድ የኢራን መርከቦች የአሜሪካን ክትትል ለማምለጥ በፓኪስታንና ህንድ በኩል ረጅም እና ውድ መንገዶችን በመጠቀም ነዳጁን ለቻይና ለማድረስ እየሞከሩ ሲሆን፣ ፔንታጎን በበኩሉ እርምጃው ኢራን ሽብርተኝነትን ለመደገፍ የምትጠቀምበትን የገቢ ምንጭ ለመምታት የታለመና ውጤታማ ነው ብሎታል።
ይህ በሁለቱ ሀገራት መካከል ያለው የንግድ መስመሮችን እንደ ጦር መሳሪያ የመጠቀም እንቅስቃሴ፣ ቀጠናውን ወደ "ቀዝቃዛ ጦርነት" ምዕራፍ እያሸጋገረው መሆኑን ተንታኞች ስጋታቸውን እየገለጹ ይገኛሉ።
02/05/2026
|
ወጋገን ሞባይል መተግበሪያን ከጎግል ፕሌይ ወይም ከአፕ ስቶር በማውረድ አልያም *866 # በመጠቀም በማንኛውም ጊዜ እና ቦታ ሂሳብዎን በምቾት ያንቀሳቅሱ።
https://play.google.com/store/apps/details?id=com.act.wegagen
https://apps.apple.com/in/app/wegagen-mobile/id6472656143
ለተጨማሪ መረጃ በ866 ነፃ የስልክ መስመር ወደ ደንበኞች ግንኙነት ማዕከል ይደውሉ፣ ይስተናገዱ::
Follow us and get more information...
https://linktr.ee/WegagenBank
02/05/2026
በኡጋንዳ ተቃውሞን ያፍናል የተባለዉና እስከ 20 ዓመት እስራት የሚያስቀጣው አዋጅ ከፍተኛ ውዝግብ አስነሳ
በኡጋንዳ ፓርላማ በአስቸኳይ እየታየ ያለውና "የሉዓላዊነት ጥበቃ አዋጅ 2026" ተብሎ የተሰየመው አዲስ ረቂቅ ሕግ በሀገሪቱ የፖለቲካ ምህዳር እና በዓለም አቀፍ ለጋሽ ድርጅቶች ዘንድ ከፍተኛ ውዝግብ እና ስጋት ፈጥሯል።
ይህ ረቂቅ አዋጅ "የውጭ አገር ጥቅሞችን" ሲያራምዱ የተገኙ ግለሰቦች እና ተቋማት እስከ 20 ዓመት በሚደርስ ጽኑ እስራት እንዲቀጡ የሚደነግግ ሲሆን፣ በተለይም በውጭ እርዳታ ላይ ለሚደገፉ የሲቪክ ማኅበራት እና የተቃዋሚ ፓርቲዎች ህልውና ላይ ትልቅ አደጋ ደቅኗል ተብሏል።
አዋጁ ማንኛውም ድርጅት ወይም ግለሰብ በ12 ወራት ውስጥ ከውጭ አገር የሚቀበለው የገንዘብ ድጋፍ ከ400 የኡጋንዳ ሽልንግ እንዳይበልጥ ጥብቅ ገደብ ይጥላል።
ይህ ገደብ በተለይ በጤና፣ በትምህርት እና በሰብአዊ መብት ተሟጋችነት ላይ የሚሰሩ ድርጅቶችን ሥራ ሽባ ሊያደርግ እንደሚችል ተገልጿል።
የኡጋንዳ የሕግ ባለሙያዎች ማኅበር አዋጁን "ሕገ-መንግሥታዊ መፈንቅለ መንግሥት" ሲል የጠራው ሲሆን፣ ዓላማውም በመንግሥት ላይ የሚሰነዘሩ ተቃውሞዎችን ማፈን እና ነጻ የሲቪክ ማኅበራትን ማጥፋት ነው ሲል ኮንኖታል።
የኡጋንዳ ተቃዋሚ መሪ ኢዩኤል ሴንዮኒ በበኩላቸው፣ "ይህ ሕግ የሩሲያ እና የቻይና አፋኝ ሕጎች ግልባጭ ነው" ሲሉ መንግሥትን ወቅሰዋል።
የዓለም ባንክ ለኡጋንዳ ፓርላማ በላከው ይፋዊ ደብዳቤ፣ አዋጁ በመደበኛ የልማት ሥራዎች ላይ የተሰማሩ ዓለም አቀፍ ድርጅቶችን እንደ "ውጭ አገር ወኪል" በመፈረጅ ለወንጀል ክስ ሊዳርጋቸው እንደሚችል አስጠንቅቋል።
ኡጋንዳ በጤና እና በትምህርት ዘርፍ በከፍተኛ ሁኔታ በውጭ እርዳታ ላይ የምትመካ በመሆኗ፣ ይህ አዋጅ በሀገሪቱ ኢኮኖሚ እና ማኅበራዊ አገልግሎቶች ላይ ከፍተኛ ጉዳት ሊያደርስ እንደሚችል የኢኮኖሚ ባለሙያዎች ይናገራሉ።
ፕሬዝዳንት ዩዌሪ ሙሴቪኒ ስለ አዋጁ የሚነሱ ስጋቶችን "ጫጫታ" ሲሉ አጣጥለዋል።
ፕሬዝዳንቱ በሰጡት መግለጫ፣ ኡጋንዳ የውጭ ኃይሎች መጫወቻ መሆን የለባትም ካሉ በኋላ "ሉዓላዊነት ማለት እባካችሁ ብቻችንን ተዉን ማለት ነው" ሲሉ አዋጁ ለሀገር ደህንነት አስፈላጊ መሆኑን አጽንተው ተናግረዋል።
ይህ አዋጅ ፕሬዝዳንት ሙሴቪኒ ግንቦት 4 ቀን 2018 ዓ.ም ለስድስተኛ ጊዜ ለሚካሄደው የቃለ መሃላ ሥነ-ሥርዓት ከመድረሳቸው በፊት በፓርላማው ጸድቆ ሥራ ላይ ይውላል ተብሎ ይጠበቃል።
02/05/2026
FSD Ethiopia CEO Hikmet Joins INPRF Board to Shape Global NPO Reporting
The International Non-Profit Reporting Foundation (INPRF), formerly known as IFR4NPO, has announced the appointment of Hikmet Abdella, CEO of Financial Sector Deepening (FSD) Ethiopia, as a member of its board.
This appointment brings a prominent Ethiopian expert to the global stage as the international foundation works to implement the first-ever International Non-Profit Accounting Guidance (INPAG), specifically designed for non-profit organizations.
Hikmet is a seasoned professional with extensive experience in the finance and regulatory sectors. Prior to leading FSD Ethiopia, she served as the Director General of the Accounting and Auditing Board of Ethiopia (AABE).
Read More (https://capitalethiopia.com/2026/05/02/fsd-ethiopia-ceo-hikmet-joins-inprf-board-to-shape-global-npo-reporting/)
01/05/2026
የሀገር በቀል ቴክኖሎጂ ውጤቶችን ለችግር ፈቺነት የሚያውል አዲስ የለውጥ ስነ-ምህዳር ይፋ መደረጉ ተሰማ
በኢትዮጵያ ወጣቶች ዘንድ የሚገኙ የፈጠራና የቴክኖሎጂ ስራዎችን በማቀናጀት ለሀገር ኢኮኖሚ ግንባታ እንዲውሉ የሚያስችል አዲስ የለውጥ ስነ-ምህዳር በክሪኤቲቭ ኪንግደም ይፋ መደረጉ ተገለፀ።
ይህ አዲስ ፕሮግራም ይፋ የሆነው በዓለም አቀፍ የላብ አደሮች ቀን ሲሆን፣ ዋና ዓላማውም ወጣቶች ያላቸውን የአእምሮ ውጤት፣ ሀገር በቀል ቴክኖሎጂዎችንና የፈጠራ መፍትሄዎችን በመጠቀም ማህበራዊና ኢኮኖሚያዊ ዕድገትን ማረጋገጥ እንደሆነ ተገልጿል።
የክሪኤቲቭ ኪንግደም ዋና ስራ አስኪያጅ አቶ ታደሰ ኃይሉ እንደገለጹት፤ ፕሮግራሙ ኢትዮጵያውያን ወጣቶች ያላቸውን ዕውቀት ወደ አደባባይ አውጥተው ለራሳቸውና ለሌሎች ዜጎች የስራ ዕድል እንዲፈጥሩ እንዲሁም የሀገሪቱን ችግር በራሷ ልጆች ዕውቀት ለመፍታት ታስቦ የተቀረጸ ነው።
ፕሮግራሙ በሳይንሳዊ መሠረት ላይ የተገነባ በመሆኑ ኢትዮጵያ በዓለም አቀፍ የቴክኖሎጂና ፈጠራ ኢኮኖሚ ውስጥ ተሳታፊ እንድትሆን ትልቅ በር ይከፍታል ተብሎ እንደሚጠበቅ ካፒታል ከተቋሙ የደረሰው መረጃ ያመልክታል።
በቀጣዮቹ አምስት ዓመታት ውስጥ ቁጥራቸው ቀላል የማይባል ዜጎችን ተጠቃሚ ለማድረግና ሰፊ የስራ ዕድል ለመፍጠር ግብ የተቀመጠ ሲሆን፣ ፕሮግራሙ በብሔራዊ ደረጃ የተቀናጀ እንቅስቃሴ በማድረግ የስራ ፈጣሪዎችንና አጋሮቻቸውን በሀብትና በዕውቀት ለመደገፍ መዘጋጀቱም ተመላክቷል።
የፈጠራ ሀሳብ ያላቸው ወጣቶች በድርጅቱ ድረ-ገጽ አማካኝነት አስፈላጊውን መረጃ ማግኘት እንደሚችሉና በቅርቡ በሚጀመረው የመጀመሪያው ምዕራፍ መመዝገብ እንደሚችሉ ተገልጿል።
01/05/2026
በኢራን ጦርነት አሜሪካ እስከ 2.8 ቢሊዮን ዶላር የሚገመት የጦር መሣሪያ አጣች
በኢራን እና በአሜሪካ-እስራኤል ጥምረት መካከል እየተካሄደ ባለው ጦርነት አሜሪካ ከ2.3 እስከ 2.8 ቢሊዮን ዶላር የሚገመት የአየር ላይ የጦር መሣሪያ ኪሳራ እንደደረሰባት በዋሽንግተን የሚገኘው የስትራቴጂክ እና ዓለም አቀፍ ጥናት ማዕከል (CSIS) ይፋ አደረገ።
ጥናቱ እንደሚያመለክተው፣ ጦርነቱ ከተጀመረበት ባሉት 61 ቀናት ውስጥ የኢራን ሚሳኤሎችና ድሮኖች የአሜሪካን የተራቀቁ የራዳር ሥርዓቶች እና የጦር አውሮፕላኖች ኢላማ አድርገዋል።
በተለይም በሳዑዲ አረቢያ የሚገኘው የፕሪንስ ሱልጣን አየር ኃይል ጣቢያ ላይ በደረሰ ጥቃት 700 ሚሊዮን ዶላር የሚያወጣውና እንደ በራሪ የዕዝ ማዕከል የሚያገለግለው ‘E-3 AWACS’ የተሰኘው የራዳር አውሮፕላን መውደሙ ለፔንታጎን ትልቅ ድንጋጤ መፍጠሩ ተመልክቷል።
የአሜሪካ መከላከያ ሚኒስትር የኢራን ወታደራዊ አቅም በታሪክ ታይቶ በማይታወቅ ፍጥነት መዳከሙን ቢገልጹም፣ መሬት ላይ ያለው እውነታ ግን ተቃራኒ መሆኑን የዘርፉ ተንታኞች ይናገራሉ።
በጦርነቱ ወቅት እስከ አንድ ቢሊዮን ዶላር የሚገመቱ የ‘THAAD’ ሚሳኤል መከላከያ ራዳሮች መውደማቸውና በኩዌት ውስጥ በደረሰ ጥቃት ሦስት የF-15 የጦር ጄቶች መከስከሳቸው የኪሳራውን መጠን ከፍ አድርጎታል።
የአሜሪካ መንግሥት የጉዳቱን መጠን ለሕዝብ ይፋ ከማድረግ ቢቆጠብም፣ ይህ ሁኔታ በመጪው የኅዳር ወር የአጋማሽ ዘመን ምርጫ ላይ በፕሬዚዳንት ዶናልድ ትራምፕ አስተዳደር ላይ ከፍተኛ የፖለቲካ ጫና ሊያሳድር እንደሚችል ተገምቷል።
30/04/2026
ባይናንስ በኢትዮጵያ ብር የሚደረጉ የክሪፕቶ ግብይቶችን ሊያቆም መሆኑን አስታወቀ
በዓለማችን ግዙፉ የክሪፕቶ ምንዛሬ ግብይት መድረክ የሆነው ባይናንስ ፣ ከግንቦት 7 ቀን 2018 ዓ.ም ጀምሮ በኢትዮጵያ ብር የሚከናወኑ የ“እርስ-በእርስ” የንግድ አገልግሎቶችን እንደሚያቋርጥ ይፋ አደረገ።
ተቋሙ ይህንን ውሳኔ ያስተላለፈው ከሀገሪቱ የፋይናንስ ተቆጣጣሪ አካላት የቀረበበትን ተፅዕኖ ተከትሎ መሆኑን ገልጿል።
ይህ ውሳኔ የተሰማው፣ የኢትዮጵያ ብሔራዊ ባንክ ከሁለት ወራት በፊት በሀገሪቱ ብር የሚደረጉ ማናቸውም የክሪፕቶ ምንዛሬ ግብይቶች "ሕገ-ወጥ" መሆናቸውን በመግለጽ የሕዝብ ማስጠንቀቂያ ካወጣ በኋላ ነው። እንደ ብሔራዊ ባንክ መመሪያ፣ ከማዕከላዊ ባንኩ ዕውቅና ውጪ በብር የሚደረግ ማንኛውም የክሪፕቶ ግብይት በጥብቅ የተከለከለ ነው።
ዝርዝሩን ያንብቡ
https://capitalethiopia.com/2026/04/30/binance-announces-suspension-of-crypto-trading-services-birr/
30/04/2026
Dashen Breweries Appoints Its First Ethiopian CEO
Dashen Breweries SC Board of Directors has announced the appointment of Matyas Getachew as its new Chief Executive Officer, effective on April 27, 2026.
This appointment is regarded as a historic milestone for the sector, as he becomes the first Ethiopian CEO to lead a major company in a brewing industry that has historically been dominated by expatriate leadership.
Matyas joined Dashen in 2020 as Chief Financial Officer (CFO), where he played a pivotal role in strengthening the company’s financial position, supporting strategic decisions, and establishing robust operational systems.
https://www.facebook.com/61583580063180/posts/122136633435119335/
Click here to claim your Sponsored Listing.
Category
Contact the business
Telephone
Website
Address
Bole Behind Rwanda Embassy
Addis Ababa
P.O.BOX95CODE1110