NAOD Multimedia
ናኦድ መልቲሚዲያ፣ለብዙሃን መትረፍያ�
21/08/2024
#ኢራን
ኢራን በአስገድዶ መድፈር ወንጀል ጥፋተኛ የተባለን ወንጀለኛ በስቅላት ገድላለች።
በማዕከላዊ ኢራን " ዝድ ክልል "አስገድዶ መድፈር መፈጸሙ በፍርድ ቤት የተረጋገጠበት ግለሰብ ሞት ተቀጥቷል።
ግለሰቡ " በጥንቆላ ይተዳደራል " የተባለ ሲሆን ወደሱ የሚመጡ ሴቶችን በማታለል አስገድዶ ሲደፍር እንደነበር ተገልጿል፡፡
ከ12 በላይ የክስ መዝገቦች የተከፈቱበት ይህ ሰው አሱን ጨምሮ ከነ ረዳቱ ጥፋተኛ ሆነው ተገኝተው በሞት ፍርድ እንዲቀጡ ውሳኔ ተላልፎባቸዋል፡፡
በፍርድ ቤቱ ውሳኔ መሰረትም ጥፋተኛ የተባሉት ሰዎች ታንቀው እንዲገደሉ ተደርጓል።
ኢራን በአስገድዶ መድፈር ወንጀል ጥፋተኛ በተባሉ ወንጀለኞች ላይ ከባድ ቅጣት ከሚጥሉ ሀገራት መካከል አንዷ ናት።
መረጃው የአን አይን ኒውስ / አል አረቢያ ነው።
https://t.me/Naod_multimidea
21/08/2024
ለህፃን ሄቨን እናት የመኖሪያ ቤት ተሰጠ
የአዲስ አበባ ከተማ አስተዳደር ልጇን በግፍ ለተነጠቀቸው ሕጻን ሄቨን እናት የመንግስት መኖሪያ ቤት አበርክቷል፡፡
የአዲስ አበባ ከተማ አስተዳደር ከንቲባ አዳነች አቤቤ እና የከተማ አስተዳደሩ ከፍተኛ አመራሮች ዛሬ የሄቨንን እናት በማግኘት አጽናንተዋል::
ልጇን በግፍ ተነጥቃ ባለፈው አንድ ዓመት ፍትሕ ሳታገኝ ለቆየችው ሲስተር አበቅየለሽ የፍትሕ ሒደቱን ለመከታተል ፣ያለችበት ሁኔታ የተሻለ እንዲሆንላትና ተጋላጭነቷን ለመቀነስ እንዲመች የከተማ አስተዳደሩ አንድ የመንግስት መኖሪያ ቤት አበርክቷል፡፡
ከዚህ ባለፈም በሙያዋ በአዲስ አበባ ከተማ ውስጥ እንድትሰራ መመቻቸቱን ነው ከንቲባ አዳነች የገለጹት፡፡
የህፃን ሄቨን ጉዳይ የሁላችንም ጉዳይ በመሆኑ ድርጊቱ ተገቢውን ፍትህ ማግኘቱ የሌሎች ህፃናት ተጋላጭነትን ለመቀነስ አስተዋፅዖ ያለው ነው ብለዋል ከንቲባዋ፡፡
የዚህ አይነት ጭካኔ የተሞላበት ድርጊት እንዳይፈፀም የማህበረሰቡ የአመለካከት ለውጥ እንዲመጣ እና ችግሩ የጋራ ጉዳይ በመሆኑ ሁሉም ሃላፊነቱን ሊወጣ ይገባልም ሲሉም ጥሪ አቅርበዋል፡፡
https://t.me/Naod_multimidea
17/08/2024
በአንዳንድ ''አውሬዎች'' ምክንያት ወንድ ሆነን (በፆታ) በመፈጠራችን እንሸማቀቅ? ወንድነታችንን እንጥላው? እንርገመው ይሆን?
ሰው ሆኖ መፈጠር በራሱ ልዩ ነገር ነው። ወንድ ወይ ሴት ሆኖ መወለድ ደግሞ የፈጣሪ ውብ ስጦታ/ፀጋ ነበር። ግን በቃ ''ነበር'' ነው!
እንዲህ ያለ ከምድራዊ ብቻ ሳይሆን ከሰማያዊ/ተፈጥሯዊ ሕግ ጋር መጋጨት ከየት፤ እንዴት የመጣብን ጉድ ነው?
በዚህች እንቡጥ ሕፃን ጉዳይ ትክክለኛውን ነገር ማወቅ እንፈልጋለን። #ፍትሕ እንሻለን!
ይህችን እምቦቀቅላ ልጅ ''ነፍስ ይማር'' ማለትስ አይከብድም? አምጣ ወልዳ፤ በችግር ተፈትና ላሳደገች እናቷ ፅናቱን ተመኘሁ! ይህንን እያዩ/እየሰሙ ለሚያድጉ ሕፃናት ስንል ግን የሆነ ማህበራዊ ፍትሕ ማበጀት አለብን። ሞራል የሚባል ነገር ቀርቷል!
S**o Lema
ኢትዮጵያ🇪🇹🤝🤝
full video 👉👉tiktok.com/.a.t.c.h
ድሬ🤝ጉራጌ🤝ሸገር🙌
Full video 👉tiktok.com/.a.t.c.h
ሼር አድርጉት🙏
ቤተሰቦንና ወዳጅዎን እናፋልጎ🙌
boom 🔥🔥🔥🔥🔥
tiktok.com/.a.t.c.h
Click here to claim your Sponsored Listing.
Category
Website
Address
Addis Ababa