Imam Tefera
كل نفس ذاقت الموت!
ነፍስ ሁሉ ሞትን ቀማሽ ናት!
ሚሽነሪዎች ኢየሱስ ብርሃን ተብሏል ስለዚህ በቁርአንና በኢየሱስ ንግግር ፈጣሪ የተባለው ኢየሱስ ነው ብለው አረፉት፦
ዮሐንስ 8፥12 ደግሞም ኢየሱስ፦ "እኔ የዓለም ብርሃን" ነኝ፤
እኛም ምግታችንን ሰፋ አድርገን ታዲያ ኢየሱስ የዓለም ብርሃን መባሉ አምላክ ያሰኘዋልን? ብለን ጥያቄ እናቀርባለን፤ መልሱ አዎ ከሆነ እንግዲያውስ ብዙ አምላኮች ሊኖሩ ነው፤ ምክንያቱም የዓለም ብርሃን የተባለው ኢየሱስ ብቻ ሳይሆን ሃዋርያትም ጭምር ናቸው፦
ማቴዎስ 5፥14 " " ናችሁ።
አይ ሃዋርያትን ብርሃን ያደረጋቸው እግዚአብሔር ስለሆነ የእነርሱ ብርሃንነት በመደረግ የተመሰረተ የፀጋ እንጂ የባህርይ አይደለም ከተባለ ኢየሱስንስ ብርሃን ያደረገው እግዚአብሔር አይደለምን? ስለዚህ የኢየሱስ ብርሃን መሆን እንደ ሃዋርያት በፀጋ እንጂ የባህርይ አይደለም፦
ኢሳይያስ 49፥6 እርሱም፦ የያዕቆብን ነገዶች እንድታስነሣ ከእስራኤልም የዳኑትን እንድትመስል ባሪያዬ ትሆን ዘንድ እጅግ ቀላል ነገር ነውና እስከ ምድር ዳር ድረስ መድኃኒት ትሆን ዘንድ ለአሕዛብ ""ብርሃን አድርጌ"" ሰጥቼሃለሁ ይላል።
ኢሳይያስ 42፥7 እኔ እግዚአብሔር በጽድቅ ጠርቼሃለሁ፥ እጅህንም እይዛለሁ እጠብቅህማለሁ፥ የዕውሩንም ዓይን ትከፍት ዘንድ የተጋዘውንም ከግዞት ቤት በጨለማም የተቀመጡትን ከወህኒ ቤት ታወጣ ዘንድ ለሕዝብ ቃል ኪዳን ለአሕዛብም ""ብርሃን አድርጌ"" እሰጥሃለሁ።
26/07/2022
ፈጣሪ(አምላክ)በሰራው (በወሰነው) ውሳኔ እንደሰው ልጅ ይፀፀታል? ወይስ አይፀፀትም?
➖➖➖➖➖➖➖➖➖➖➖➖
1✅“ሐሰትን ይናገር ዘንድ እግዚአብሔር ሰው አይደለም፥ #ይጸጸትም ዘንድ የሰው ልጅ አይደለም።”
— ዘኍልቁ 23፥19
¶
2✅“እግዚአብሔርም ሰውን በምድር ላይ በመፍጠሩ #ተጸጸተ፥ በልቡም #አዘነ።”
— ዘፍጥረት 6፥6
ዕውን አምላክ (ፈጣሪ) እንደ ሰው ልጅ ያዝናልን?
¶
“እግዚአብሔርም ስለዚህ ነገር #ተጸጸተ፤ ይህ አይሆንም፥ ይላል እግዚአብሔር።”
— ትንቢተ አሞፅ 7:3
ዕውን አምላክ (ፈጣሪ) እንደ ሰው ልጅ ይፀፀታልን?
¶
3✅“በፊቴ ክፉን ነገር ቢያደርግ ቃሌንም ባይሰማ፥ እኔ አደርግለት ዘንድ ስለ ተናገርሁት መልካም ነገር #እጸጸታለሁ።”
— ኤርምያስ 18፥10
ዕውን አምላክ (ፈጣሪ) እንደ ሰው ልጅ ይፀፀታልን?
¶
4✅“የእግዚአብሔርም ቃል፦ ሳኦል እኔን ከመከተል ተመልሶአልና፥ ትእዛዜንም አልፈጸመምና ስላነገሥሁት #ተጸጸትሁ ብሎ ወደ ሳሙኤል መጣ።”
— 1ኛ ሳሙኤል 15፥10-11
ዕውን አምላክ (ፈጣሪ) እንደ ሰው ልጅ ይፀፀታልን?
¶
5✅“እግዚአብሔርም ያጠፋት ዘንድ ወደ ኢየሩሳሌም መልአክን ሰደደ፤ ሊያጠፋትም በቀረበ ጊዜ እግዚአብሔር አይቶ ስለ ክፉው ነገር #ተፀጸተ።”
— 1 ዜና 21፥15
ዕውን አምላክ (ፈጣሪ) እንደ ሰው ልጅ ይፀፀታልን?
¶
6✅“እግዚአብሔርም በሕዝቡ ላይ ሊያደርግ ስላሰበው ክፋት #ራራ።”
— ዘጸአት 32፥14
ዕውን አምላክ (ፈጣሪ) እንደ ሰው ልጅ ይፀፀታልን?
¶
7✅“የእግዚአብሔርም መልአክ ኢየሩሳሌምን ያጠፋት ዘንድ እጁን በዘረጋ ጊዜ እግዚአብሔር ስለ ክፉው ነገር #አዘነ፥”
— 2ኛ ሳሙኤል 24፥16
ዕውን አምላክ (ፈጣሪ) እንደ ሰው ልጅ ይፀፀታልን?
¶
8✅“እግዚአብሔርም፦ የፈጠርሁትን ሰው ከምድር ላይ አጠፋለሁ፥ ከሰው እስከ እንስሳ እስከ ተንቀሳቃሽም እስከ ሰማይ ወፍም ድረስ ስለ ፈጠርኋቸው #ተጸጽቼአለሁና አለ።”
— ዘፍጥረት 6፥7
ዕውን አምላክ (ፈጣሪ) እንደ ሰው ልጅ ይፀፀታልን?
¶
9✅“እግዚአብሔርም በእስራኤል ላይ ሳኦልን ስላነገሠ #ተፀፀተ።”
— 1ኛ ሳሙኤል 15፥35
ዕውን አምላክ (ፈጣሪ) እንደ ሰው ልጅ ይፀፀታልን?
¶
10✅“ይህ ስለ እርሱ የተናገርሁበት ሕዝብ ከክፋቱ ቢመለስ፥ እኔ አደርግበት ዘንድ ካሰብሁት ክፉ ነገር #እጸጸታለሁ።”
— ኤርምያስ 18፥8
ዕውን አምላክ (ፈጣሪ) እንደ ሰው ልጅ ይፀፀታልን?
‼Note:–
ከላይ በጥቂቱ በተመለከትናቸው 10 ያህል የመፅሀፍ ቅዱስ ጥቅሶች (አንቀፆች) መሰረት "ፈጣሪ ወዶና ፈቅዶ ከሰራ (ከወሰነ) በኋላ ፈጣሪ በስራው እንደ ሰው ልጅ ይፀፀታል?
❓ወይስ ፈጣሪ (አምላክ) አይፀፀትም?❓
የመፅሀፍ ቅዱስ የርስ በርስ ግጭቶችን አስታርቁልን እስኪ
28/06/2022
ያው በረሐ ላይ ነን…!!
🔥🔥🔥🔥
በቶሌ በአንድ መስጊድ ውስጥ ብቻ 40 ሰው ነው የተገደለው። እኔ ቤት ውስጥ 12 ሰው ሞተ። ሌላው ቆስሎ ወጣ። ያው በረሐ ላይ በእግር እየሄድን ነው መድረሻ አጥተን። ሁለት ልጆች ተርፈውልኝ ነበር በውሃ ጥም ተቸግረናል።
ከጥቃቱ የተረፉ አንድ አዛውንት ለDW Amharic የተናገሩት::
አላህ ሆይ ! እርዳታህን!!
የኦሮሚያ ክልል እስልምና ጉዳዮች ጠቅላይ ምክር ቤት የአስቸኳይ ጠቅላላ ጉባኤ የአቋም መግለጫ
*****
1. ህዝባችን ሁል ጊዜ ደህንነታቸውን መጠበቅ አለባቸው። ከሌሎች ሀይማኖቶች እና ብሄር ብሄረሰቦች ጋር መግባባት እና በሰላም አብሮ መኖር የሀይማኖታችን መሰረት ነው። የሀገርና የህዝብን ደህንነት የመጠበቅ ሃይማኖታዊ ግዴታ አለብን። ተቋማችን ለማስተካከልም ሆነ ሃይማኖታዊ መብታችንን ለማስጠበቅ በምንታገልበት ግዜ እያንዳንዱ የሀገራችን ዜጋ መብቱን ማክበር እና በሰላም አብሮ መኖር አለብን። ስለሆነም ህዝባችን ከፀጥታ አካላት ጋር ተስማምቶ የክልሉንና የሀገሪቱን ፀጥታ እንዲጠብቅ ጥሪያችንን እናቀርባለን።
2. እኛ ሙስሊሞች ነን። የሙስሊም አንድነት ሁሌም አስፈላጊ ነው። በተለይ ጠላት በተለያዩ ሴራዎች አንድነታችንን ለማፍረስ በሚሞክርበት ወቅት አንድነታችን መጠናከር አለበት። አንዴ ሱፊ ሰለፊ እያሉን፣ ሌላ ጊዜ ነባሩ እና መጤ እስልምና በማለት ከፋፍለውናል። ሌሎችም ብዙ ስሞችን ሰጥተውናል። ይህ ድርጊት ኢስላማዊውን ህግ የሚጻረር እና ሙስሊሙን ኡማ የሚያፈርስ ነው። ድርጊቱን በፅኑ እያወገዝን ህዝቡ የውስጥና የውጭ ጠላቶችን ሴራ ለማክሸፍ በቁርኣንና ሀዲስ ላይ የተመሰረተ አንድነታችንን አጠናክረን እንድንቀጥል ጥሪያችንን እናቀርባለን።
3. የኦሮሚያ መጅሊስ ስራ አስፈፃሚ ኡለማዎች እና የስራ አመራር ቦርድ ላይ ክፍተቶች እንዳሉ ይታወቃል። ይህን ክፍተት አሟልተናል። አዲሱን የምክር ቤት ፕሬዝዳንትም መርጠን በሙሉ ድምፅ አፅድቀናል።
4. በተለያዩ የሀገራችን ክፍሎች እየተፈጸመ ያለውን አሰቃቂ ግድያ ሁሉ እናወግዛለን። በተለይ ሰሞኑን በአማራ፣ በጋምቤላ፣ በቤኒ ሻንጉል፣ በራሳችን ክልል በምዕራብ ወለጋ ላይ የተፈፀመው ዘግናኝ ግድያ ከልብ አሳዝኖናል። ህይወታቸውን ለማትረፍ ወደ መስጂድ የተሰደዱትን ህዝበ ሙስሊሙን መግደል ጨካኝ እና ኢሰብአዊ ድርጊት ነው። መሰል ድርጊቶች በአማራ ክልል እና በወለጋ በተለያዩ ጊዜያት በተደጋጋሚ ተፈጽመዋል። እነዚህ ግድያዎች ብዙዎቹ በሙስሊሞች ላይ ያተከሩ መሆናቸው ደግሞ ሌላ ስጋት ፈጥሮብናል። ይህ ድርጊት እንደ ሰብአዊም ሆነ እንደማንኛውም ሀይማኖት ዘግናኝ ወንጀል ነው። መንግስት የማያዳግም እርምጃ በመውሰድ ያለፈውንም ሆነ የአሁኑን ግድያ ለህዝቡ እንዲያሳውቅ እናሳስባለን። እንደ ኦሮሚያ ክልል እስልምና ጉዳዮች ምክር ቤት በሙስሊሞች ላይ እየደረሰ ያለውን ተደጋጋሚ ግድያ በእጅጉ አሳስቦናል። እናም ይህንን በጎሳና በሃይማኖት እየከፋፈለ ዜጎችን እየገደለ ያለውን ድርጊት መንግስት ትኩረት እንዲሰጠው እናሳስባለን።
5. የኢትዮጵያ እስልምና ጉዳዮች ጠቅላይ ምክር ቤት ሆነው የተመረጡትን አዲስ የሽግግር መሪዎች በሙሉ ድምፅ እንደግፋለን። እንደሚታወቀው የኢትዮጵያ ሙስሊሞች እነሱን የሚተካ ጠንካራ ተቋም ለማግኘት ለረጅም ጊዜ ሲታገሉ ቆይተዋል። በሽግግር ወቅት በርካታ የህዝብ ጥያቄዎች በተመለሱበት ጊዜ መጅሊሱ ይህንን እድል ተጠቅሞ በተወሰነ ደረጃ ለማሻሻል ተሞክሯል። መጅሊስ በአዋጅ መቋቋሙ ለኢትዮጵያ ሙስሊሞች ትልቅ እድል ነበር። ለዚህም ስባል የሽግግር መንግስቱን በተለይም ጠቅላይ ሚኒስትሩን ደጋግመን እናመሰግናለን። ነገር ግን የቀድሞው የሽግግር መጅሊስ አመራሮች ተቋሙን ከህዝበ ሙስሊሙ ተቃራኒ አቅጣጫ በመውሰድ ህዝቡ ለብዙ ዙር መራራ ትግል ልጋለጥ ችለዋል። በመሆኑም የፌደራል መጅሊስ ኡለማዎች እና የስራ አመራር ቦርድ አባላት ከፍተኛ ትግል በማድረግ ህጋዊ ጠቅላላ ጉባኤ በማካሄድ ሀሉን ያቀፈ አመራር መርጠዋል። ነገር ግን አመራሩ የመጅሊስን ግቢ ሳይረከብ አንድ ወር ሊሞላው ተቃርቧል። ይህንን ህጋዊ ውሳኔ ተግባራዊ ለማድረግ የህግ የበላይነትን ማስከበር ከመንግስት ይጠበቃል። ስለሆነም መንግስት ህግ አስከብሮ የህዝቡን ጥያቄ በፍጥነት እንዲመልስ እና የመጅሊሱን ግቢን ለህጋዊው አካል እንዲያስክብ እንጠይቃለን።
6. በፌደራል መጅሊስ ውስጥ ስልጣን የተቆጣጠረው ህገወጥ አመራር በኦሮሚያ መጅሊስ እና በክልሉ ሙስሊሞች ላይ የሚያደርሰውን የስም ማጥፋት ዘመቻን አጥብቀን እናወግዛለን። እንደሚታወቀው በህጋዊ መንገድ ከስልጣን የተነሱ የፌደራል መጅሊስ የቀድሞ አመራሮች በስልጣን ፍቅር ሰክረው በስልጣኑ ለመቆየት ያልተጠቀሙበት ስልት የለም። ጠቅላይ ሚኒስትሩን ጨምሮ ከ120 በላይ ሙስሊሞች በተገኙበት ደም ይፈሳል እንጅ ከስልጣን አልወርድም ሲሉ የቀድሞ ፕሬዝዳንት ተናግረዋል። የኦሮሚያ መጅሊስን ደግሞ በመቶዎች የሚቆጠሩ ኢማሞችን አባረረ፣ የመስጂድ ኮሚቴዎችን አፈናቅሏል፣ ወሃብያዎች ብዙ ሰዎችን በድንጋይ እየገደለ ነው ይላሉ። የኦሮሚያ መጅሊስ አንድም ኢማም አላባረረም፣ የመስጂድ ኮሚቴም አላፈናቀለም። የኦሮሚያ ሙስሊሞችም የተከበሩ ህዝቦች ናቸው። ስማቸው ሙስሊሞች እንጂ ወሃቢዎች አይደለም። እንደዚህ አይነት መጥፎ ሥራዎችንም አይሠሩም። በቀድሞው የፌዴራል መጅሊስ አመራር በኦሮሚያ መጅሊስ እና በክልሉ ሙስሊሞች ላይ የሚደረገው የስም ማጥፋት ዘመቻ በሌሎች ሀይማኖቶች ተከታዮች እና በፖለቲካ ሚዲያዎችም ጭምር እየተካሄደ ይገኛል። እነዚህን ሁሉ የስም ማጥፋት ድርጊቶችን አጥብቀን እያወገዝን መንግስት እነዚህን ሁሉ አጥፊዎች ለፍርድ እንዲያቀርብ እንጠይቃለን።
7. እንደሚታወቀው የፌደራል መጅሊስ አዲሶቹ አመራሮች የመጅሊሱን ግቢ እስካሁን አልተረከቡም። ስለሆነም የሐጅ ተጓዦች እየተስተናገዱ ያሉት በህገ ወጥ መንገድ በስልጣን ላይ ለመቆየት በሚጥሩ መሪዎች ነው። የነሱ አላማ ህዝበ ሙስሊሙን መከፋፈል እና ባገኘው አጋጣሚ ሁሉ በስልጣን ላይ መቆየት ነው። የሚሠሩት ሁሉ በሙስና የተበከለ ነው። በመጀመሪያ 20,000 ሰዎች ሐጅ እንዲሄዱ ተፈቅዶ ነበር፣ ነገር ግን 12,000 ሰው ለመላክ መዝግበዋል። በቀድሞው የፌዴራል መጅሊስ አመራር በአቅራቢያው ካለ ከተማ ፓስፖርት እንዳያወጡ ተደረገ። በዚህ ምክንያት ህዝቡ ወደ ፊንፊኔ መጥቶ ለከፍተኛ ወጪ ተጋልጧል። 12,000 ሰዎች ሁሉንም መስፈርት አሟልተው ከተመዘገቡ በኋላ ዶላር ስለጠፋን 3,000 ሰው ብቻ እንልካለን፣ 1,000 ሰው ተጠባባቂ ናቸው የምል መግለጫ ሰጡ። ህዝቡ ጊዜውንና ገንዘቡን እስኪጨርስ ጠብቀው ትናንት ይህንን መግለጫ ሰጡ። ይህ ማለት 8,000 ሰዎች ያለምንም ጥቅም ጊዜና ወጪን ባክነው ሐጅ ሳይሄዱ ይቀራሉ ነው። ይህ ድርጊት በእውነቱ አሳዝኖናል። ይህ ምክር ቤት ተግባራቸውን አጥብቆ እያወገዘ እነዚህን ሰዎች ለመከራ ያጋለጡ አካላት ተጣርተው ለፍርድ እንዲቀርቡ አጥብቆ ይጠይቃል።
መቼ ነው ?
ኡስታዝ አብዱልመጅድ ሁሴን አላህ ይዘንለት የዛሬ 4 ዓመት ፖስት ባደረገው ፅሁፉ መቼ ነው ? ሲል ይጠይቀናል:: ራሳችንን እንጠይቅበት :: ይሄን የጠየቀን ሰው ወደ እውነተኛ ቤቱ ሂዷል :: ራሳችንን እንጠይቅ እስኪ
*መቼ ነው* እውነተኛ ሙስሊሞች የምንሆነው?
*መቼ ነው* አላህ በፈጠራቸው ነግሮች የምንማረከው?
*መቼ ነው* አሏህ ለምን እንደፈጠርን የምንረዳው?
*መቼ ነው* አሏህ እንደሚፈልገው መኖር የምንጀምረው?
*መቼ ነው* ስለ ሀይማኖታችን በሙሉ ልብ እምንናገረው?
*መቼ ነው* እማይጠቅም ንግግር ከመናገር የምንቆጠበው?
*መቼ ነው* ሀዲስና ቁርአን ስንሰማ የምንደነግጠው?
*መቼ ነው* ለመልካም ስራ ሰበብ የምንሆነው?
*መቼ ነው* በሰላታችን የምንጠቀመው?
*መቼ ነው* ዱአችን ተሰሚነት የሚያገኝው?
*መቼ ነው* ዲናችንን የምንረዳው?
*መቼ ነው* ውሎና አዳራችን በሱና የሚሆነው?
*መቼ ነው* ሙሉ በሙሉ በአሏህ ላይ የምንመካው?
*መቼ ነው* የዱንያን ትልቅነት ከልባችን የምናወጣው?
*መቼ ነው* ቤታችን ውስጥ ያለው የተበላሸ ሂዎት የሚስተካከለው?
*መቼ ነው* ቤታችን ውስጥ ቁርአንና ሀዲስ የሚቀራው የሚወራው?
*መቼ ነው* ውሽት እምናቆመው?
*መቼ ነው* የአሏህን ውሳኔ መቃውም እምናቆመው?
*መቼ ነው* እኔ እኔ ማለት ትተን ውንደሜ እህቴ ማለት እምንጀምረው?
*መቼ ነው* ለሰዎች ከአላህ ውጪ ጌታ እንደሌለ እምንናገረው?
*መቼ ነው* በኛ ዘመን በዲናችን የበላይነት ምናገኝው?
*መቼ ነው* የኢስላም ዘቦች የምንሆነው?
*መቼ ነው* ኢስላምን የምናስተዋውቀው?
*መቼ ነው* ለድሃ እምናዝነው?.
*መቼ ነው* ትዳራችን ስላም ሚያገኝው?
*መቼ ነው* የጋብቻን ጥቅም ተገንዝበት ለትዳር የምንቻኮለው?
*መቼ ነው* ዱአቶቻችን ለገጠሩ የሚጨነቁት?
*መቼ ነው* ከሀሜት; ስውን ከመበድል; ክማስቀየምና ከማማት እምንላቀቀው?
*መቼ ነው* ወላጆቻችንን እምናስደስተውና እምንታዝዝው?
*መቼ ነው* ያልተጣራ ውሬ ካማውራት እምንቆጠበው?
*መቼ ነው* ለአሏህ ብለን እምንዋደደው?
*መቼ ነው* አሏህ በወሰነልን ነገር ደስተኞች የምንሆነው?
*መቼ ነው* የሌሊት ሰላትንና ዚክርን የምንላመደው?
*መቼ ነው* የበድለንን ይቅር የመንለው?
*መቼ ነው* ከራስ ወዳድነት እምንላቀቀው?
*መቼ ነው* ከሞት ቡኃላ ላለው ሂወት ስንቅ እምናዘጋጀው?
*መቼ ነው* ኡለማዎቻችንን እምናከብረው?
*መቼ ነው* ለእውቅት ጊዜ የምንሰጠው?
*መቼ ነው* ባወቅነው የምንሰራው?
*መቼ ነው* የ ምንሞትበትን ቀንም ይሁን ስፍራ እንደማናውቅ ተገንዝበን በተጠንቀቅ የምንቆመው?
*መቼ እረ መቼ ነው* ኢስላምን የምንኖረው?
*መቼ ነው* ለእነዚህ ተግባራዊ መልስ የምንመልሰው?
*አሏህ ያግራልን*
አብዱረሂም አህመድ
Click here to claim your Sponsored Listing.
Category
Contact the public figure
Telephone
Website
Address
Addis Ababa
Opening Hours
| 09:00 - 17:00 |