IEDC
I EDC Africa
Innovation and Entrepreneurship Development center
24/12/2023
የእንቆጳ ጉባዔ ነገ ይጀምራል
ትኩረቱን በሥራ ፈጠራ፣ ቴክኖሎጂና ኢኖቬሽን ላይ ያደረገው የእንቆጳ ጉባዔ ከጥቅምት 1 – 2 /2016 ዓ.ም በአዲስ አበባ ይካሄዳል፡፡
በሚሊኒየም አዳራሽ በሚካሄደው በዚህ ጉባኤ ሥራ ፈጣሪዎች፣ ቴክኖሎጂ አልሚዎች፣ ፖሊሲ አውጪዎች፣ ጀማሪ የንግድ ሥራ ባለሙያዎች፣ ኢንቨስተሮች እንዲሁም የትምህርትና የፋይናንስ ተቋማት ይሳተፋሉ፡፡
የጉባኤው ዓላማ ኢትዮጵያ በዲጂታል የሥራ ፈጠራ ያላትን እምቅ አቅም በማስተዋወቅ በዘርፉ የሚፈጠሩ የሥራ ዕድሎችን ማስፋት ሲሆን ለሁለት ተከታታይ ቀናት በሚካሄደው መርሃ ግብር በክህሎት ልማት፣ በሥራ ዕድል ፈጠራና ተያያዥ ጉዳዮች ላይ የፓናል ውይይቶች ይካሄዳሉ፡፡
ከውይይቶቹ ጎን ለጎንም ጀማሪ ሥራ ፈጣሪዎች ምርትና አገልግሎታቸውን የሚያስተዋውቁበት እና የገበያ ትስስር የሚፈጥሩበት ኤግዚቢሽን ይካሄዳል፡፡
መስከረም 30/2016 ዓ.ም የሥራና ክህሎት ሚኒስቴር
ለወቅታዊ ትኩስ የሥራና ክህሎት ሚኒስቴር መረጃዎች
በድረገጽ፡- http://mols.gov.et/
ፌስቡክ፡- https://www.facebook.com/MolsFDRE
ቴሌግራም፦https://t.me/fdre_mols
ቲክቶክ:- mols_official በመወዳጀት ይከታ
24/12/2023
24/12/2023
24/12/2023
በሀገራችን ለመጀመሪያ ጊዜ በፈጠራና ቴክኖሎጂ ላይ የሚሰማሩ አካላት ተቋማዊ ቅንጅት ፈጥረው ለአዳዲስ ሥራ ፈጠራና ጀማሪ ቢዝነሶች ምቹ ሥነ-ምህዳር ለመፍጠር በጋራ የሚሰሩበት The Next Ethiopian StartUp Initiative -NEST) መርሃ ግብር ማስጀመሪያ መርሃ ግብር እየተካሄደ ነው።
በማሰጀመሪያ መርሃ ግብሩ ላይ የኢፌዴሪ ም/ል ጠቅላይ ሚኒስትር ክቡር አቶ ደመቀ መኮንን፣ የሥራና ክህሎት ሚኒስቴር ክብርት ወ/ሮ ሙፈሪሃት ካሚል እና የኢኖቬሽንና ቴክኖሎጂ ሚኒስቴር ክቡር ዶ/ር በለጠ ሞላን ጨምሮ የተለያዩ ሥራ ፈጣሪዎች፣ የኢንዱስትሪ መሪዎችና ጥሪ የተደረገላቸው እንግዶች ተገኝተዋል።
ጥቅምት 13/2016 ዓ.ም የሥራና ክህሎት ሚኒስቴር
ለወቅታዊ ትኩስ የሥራና ክህሎት ሚኒስቴር መረጃዎች
በድረገጽ፡- http://mols.gov.et/
ፌስቡክ፡- https://www.facebook.com/MolsFDRE
ቴሌግራም፦https://t.me/fdre_mols
ቲክቶክ:- tiktok.com/
24/12/2023
Click here to claim your Sponsored Listing.
Category
Contact the organization
Website
Address
Addis Ababa