ETHOP
RESPECT HUMAN RIGHT AND FREEDOM. WE ALL MUST STAND AGAINST INHUMAN THREAT AND NEGATIVE RIGHTS. ALWAYS QUEST OF KNOWLEDGE AND WISEDOM.
20/02/2023
ኢትዮጵያ- በመሰዋትነት የጸናች ሀገር
የካቲት 12 ሲዘከር እናዛን ብርቱ እና ጀግና አባቶቻችንን ለማስታወስ ፤ ለሕዝብ አንድነትና ክብር የተዋደቅ ጀግኖቻቸንን ከአደዋ ዳግም ከ40 አመታት በኃላ የኢጣሊን ግፍና ወረራ ከታሪክ ማህደር መዘን እናስታዉስ፡፡
ዘመኑ እ.ኤ.ዘ.አ 19 88 ዓ.ም ከዉጫሌ ስምምነት ምክንያት የአፍሪካን የመቀራመትና የኢጣሊያኛዉ ቅጅ ሰነድ በመጻፍ ለሀያላን ሀገራት እውቅና በመቃወም ኢትዮጵያዊያን አንድ በመሆን የመጣዉ የኢጣሊን ጦር በማሸነፍ ነጻነታቸዉን ያወጁበት በኃላም ለአፍሪካ ነጻ መዉጣት ትልቅ መሰረት የጣለ ታሪካዊ ክስተት ነበር፡፡
ይህንን ሽንፈት ተከትሎ የኢጣሊ መንግስት ለ40 አመታት ኢትዮጵዮጵያን በሚሲዮን ፣ በትብብር በሚል ስበብ ሲያጠና ከቆየ በኃላ ለሽንፈት የዳረጋቸዉን የኢትዮጵያን አንድነት በማዳከም (በመጣዉ የህዝቡ አስተሳሰብ የሚሉም የታሪክ ድርሳናት እንዳሉ ልብ ይሏል) በዳግም ወረራ ለ5 አመታት ሀገሪቱን ቢቆጣጠራትም ፣ በዉስጥ አርበኞት እና በተሰራዉ የዲፕሎማሲ ስራ ሀገሪቱን ለአንደየና ለመጨረሻ ለቆ ሊሄድ ችሏል፡፡
ይህ ሲሆን በ19 29 ዓ.ም አብረሃም ደቦጭ ፣ ሞገስ አሰግዶም እና ስምኦን አደፍርስ በግራዛይኒ ላይ የጣሉት ቦንም ክፉኛ ስላቆሰለ አጸፍዉን ከ30 ሽህ በላይ የአዲስ አበባ ነዋሪዎች ላይ በግፍ ተገለዋል፡፡
የካቲት 12 ኢትዮጵያ ዳግም ሉአላዊኗን ያረጋገጠችበት ፤ ዋጋ የተከፈለላት ነች፡፡ ከዚህ ትዉልድ ከኃላ ቀር ለመዉጣ ሳይንስና ቴክኖሎጂ ፣ የዘመነ ፖለቲካ ያስፈልገዋል፡፡
ትዉልዱ በጨቋኝና ተጨቋኝ የታሪክ ፕሮፖጋንዳ ወጥቶ ለስራ ፣ ለትምህርት እና እድገት ሊተጋ ያስፈልጋል፡፡
በታሪክ የብሔር ጭቆና ሳይሆን የ ገዥ መደብ ጭቆና ነዉ፡፡ ሁሉም ሕዝብ በፌዉዳሉ ገዥ መደብ ሲበደል የነበረ ነዉ፡፡
ኢትዮጵያ የነቃ ትዉልድ ያስፈልጋታል!
ለተጨማሪ መረጃ ፡-
20/02/2023
13/02/2023
ጥያቄዉ በመንግስትዎ ለምን ዘላቂ ልማት አይረጋገጥም ? በመንግስት ዉስጥ የተለየ ፖለቲካዊ ፍላጎት ያላቸዉ ባለስልጣናት ለምን ወጥተዉ ብሔራዊ ንግግር እንዲደረግ አያደርጉም እና ብዙ ጥያቄ ቢነሳም ጠ/ሚኒሰትሩ ግን አሁንም ስለ ሀገር አንድነት ሰላምና ብልጽግና ያወራሉ፡፡
ሕዝብ ነዉ እሳቸዉን ያልተረዳዉ ወይስ እሳቸዉ ናቸዉ ሕዝብ ያልተረዱት ? የሚለዉ ግላዊ(ሳብጀክቲቨ ) ጥያቄ ነዉ፡፡
የኢትዮጵያ አየር ኃይል እና መካናይዝድ ጦር ወታደራዊ ትርኢት
15/12/2022
እስከ ህዳር ድረስ ወደ ትግራይ ክልል 82 ሽህ 2 መቶ ሽህ 19 ነጥብ 8 ሜትሪ ቶን ያልተገደበ ሰብዓዊ ድጋፍ መጓጓዙን የአደጋ ሥጋት ስራ አመራር ኮሚሽን አስታዉቋል፡፡
በመንግስት በኩል ድጋፍ የተደረገ 13 ሽህ 6 መቶ 86 ሜትሪክ ቶን ፣ መድሃኒት 12 ሽህ 2 መቶ 27 ሜትሪክ ቶን ፣ምግብ ነክ ያልሆነ 7 ሽህ 6 መቶ 51 ሜትሪክ ቶን መጓጓዙን የአደጋ ስጋት ሥራ አመራር ኮሚሽን የህዝብ ግንኙነት ኃላፊ አቶ አበበ ዘዉዴ ተናግረዋል፡፡
በጎንደር 1 ነጥብ 5 ሚሊዮን እና በአፋር ከ7 ሽህ በላይ ተፈናቃይ ለሆኑ ዜጎች በሶስት በተከፈሉ ቡድን ባለሙያ በማሰማራት እየተሰራ መሆኑን የህዝብ ግንኙነት ኃላፊዉ አክለዉ ገልጸዋል፡፡
14/12/2022
የኢትዮጵያ መንግስት እና የትግራይ አማጺ ቡድን ትህነግ የሰላም ንግግር ታሪካዊ ዘገባ፡፡
21/11/2022
የጫካ ሳተላይት ከተማ ፕሮጀክት
የጫካ ፕሮጀክት ከእንግሊዝ ኤንባሲ ጀርባ ያለውን ተረራማ ጫካ ይዞ ፣ እንጦጦን አካሎ ፣ የሱሉልታን ግርጌ ይዞ ፣ ጣፎ ደርሶ ወዲህ የሚመለስ ግዙፍ ፕሮጀክት ነው።
የቦታው ስፋት በጠቅላላ 3,700 ሄክታር ሲሆን ይህም ማለት ደግሞ የልደታ ክፍለ ከተማን አራት ያህል እጥፍ ማለት ነው - ልደታ ክፍለ ከተማ 800 ሄክታር ገደማ እንደሆነ ልብ ይሏል።
በዚህ የጫካ ሳተላይት ከተማ ውስጥ ቤተመንግስት ፣ መኖሪያ ቤቶች ፣ የንግድ ማዕከላት ፣ ግድብ ፣ትላልቅ ሰው ሰራሽ ሐይቅ ፣ የኬብል ትራንስፖርት፣ ከተማን ከተማ የሚያሰኙ መዝናኛና አገልግሎት መስጫ ግንባታዎችን ያካተተ ነው።
ከአመት በፊት የጠቅላይ ሚኒስትር ፅህፈት ቤት ባወጣው የግንባታ ተሳትፎ ፍላጎት ጥሪ 11 ኩባንያዎች ቀርበው ነበር። ከነዚህ ውስጥ የተወሰኑት እያንዳንዳቸው ከአስር ሄክታር ያላነሰ ቦታ ተረክበው በሚሰጣቸው ዲዛይን መኖሪያ አፓርትመንቶችን ለመገንባት ተንቀሳቅሰዋል።
የቤተመንግስቱም ግንባታ እየተፋጠነ እንደሚገኝ መረጃዎች ይጠቁማሉ። የቤተመንግስት ግንባታው ብቻ የየወቅቱን የኮንስትራክሽን ዋጋ ጨምሮ እስከ 80 ቢሊዮን ብር እንደሚፈጅ ፤ አጠቃላይ ሳተላይት ከተማውን ለማጠናቀቅ ደግሞ አንድ ትሪሊዮን ብር ድረስ ሊፈጅ እንደሚችል ለፕሮጀክቱ ቅርብ የሆኑ ምንጮች ይናገራሉ ።
አዲሱ-አዲስ አበባ ውብ እና በየቀኑ ብዙ ገንዘብ ማመንጨት የሚችል እንደሆነ በባለሙያዎች ታምኖበታል ። ባለሙያዎች እንደሚሉት የጫካው ከተማ ሌሎች ከተሞች ሲገነቡ የተሠሩ ስህተቶች እንዳይደገሙ እድል ይሰጣል። ሰው እና ተፈጥሮም የሚገናኙበት ውብ ስፍራም ይሆናል። ጠቅላይ ሚኒስትር ዓብይ አህመድ (phd) ለፓርላማ በሰጡት ማብራሪያ ፕሮጀክቱን ‘’የአፍሪካ ኩራት’’ ብለውታል ።
ፕሮጀክቱ በርካታ ኮንትራክተሮችን የሚያሳትፍ ፣ ብዙ የስራ ዕድል የሚፈጥር - አዳዲስ እና ዘመናዊ የአገነባብ ስልቶችን የሚያቀዳጅ በመሆኑ ለኢንዱስትሪው ተዋንያን መልካም ዜናም ጭምር ነው።
አዲሱ እየሩሳሌም -አሮጌው እየሩሳሌም ፤ አዲሱ ፓሪስ አሮጌው ፓሪስ እንደሚባለው ሁሉ አሮጌው አዲስ አበባ ፣ አዲሱ አዲስ አበባ - ይባል ዘንድ ጊዜው ፈቅዷል።
ምንጭ፡- WZ news
Click here to claim your Sponsored Listing.
Contact the business
Telephone
Website
Address
Addis Ababa
27