ECLG Church
“We preach the Gospel to bring all nations to the living God.”
ድንቅ የአምልኮ ጊዜ
#ፕሮቴስታንትመዝሙር #አምልኮ #ስብከት #ክርስቲያን #መዝሙር ChristianEncouragement
26/05/2026
አያያዥ ህይወት
ተስፋ፣ እምነት እና ፍቅር... (1ኛ ቆሮ 13፥9-13)
ማስታወስ ያለብን አንድ ነገር አለ፤ ተስፋ ያለ እምነት አይቆምም፣ እምነትም ያለ ፍቅር አይጸናም። በመጨረሻ ግን ፍቅር ብቻውን ነው ጸንቶ የሚኖረው። ❤️
ተስፋችሁ እየሞተ እንደሆነ ከተሰማችሁ ተስፋውን የሰጠውን እግዚአብሔርን እመኑት። እምነት ማለት እውር መሆን ማለት አይደለም፤ በልባችን ውስጥ የሚበራ መንፈሳዊ አይን አለውና። ተስፋችሁን በእምነታችሁ አይኖች ማየት ትችላላችሁ። 👁️
እምነታችሁ ከደከመ ደግሞ ማመን ላለብን አካል ማለትም ለእግዚአብሔር የነበረን ፍቅር ቀዝቅዞ ይሆን? ብላችሁ ራሳችሁን ጠይቁ። የፍቅር ልክ ነውና የእምነታችን አቅም። ፍቅር ፍርሃትን አውጥቶ ይጥላል። ስለዚህ የቀዘቀዘውን ፍቅራችሁን እንደገና ለማደስ ከእግዚአብሔር ጋር ያላችሁን ግንኙነት አጠንክሩ። ለዚህ ሁሉ የሚሆን የጸሎት አቅም በእግዚአብሔር ጸጋ ይጨመርላችሁ።
🙏 አሜን!!
በዚህ ሁሉ መሃል የደከማችሁት ካላችሁ፣ ይህንን አትርሱ፦
1️⃣ ስለ ተስፋ - ተስፋ የሰጣችሁ አምላክ የታመነ ነው።
2️⃣ ስለ እምነት - እናንተ ባታምኑት እንኳን እርሱ ግን ለዘላለም ታምኖ ይኖራል።
3️⃣ ስለ ፍቅር - በፍጹም ፍቅር ነው የሚወዳችሁ! ❤️
ስለዚህ ከእናንተ በኩል ተስፋ ቢሟጠጥ እንኳን፣ በእግዚአብሔር በኩል ለእናንተ ያለው ፍቅር ግን ፈጽሞ አልሞተም። አይዟችሁ፣ እግዚአብሔር ከእናንተ ጋር ነው!
18/05/2026
እግዚአብሔርን መፈለግ
(2ኛ ዜና 15 :1 - 19)
የእግዚአብሔር መንፈስ በዓዛርያስ ላይ በመጣበት ግዜ ዓዛርያስ ወደ ይሁዳ ንጉስ ወደ አሳ መጣ አሳንም እንዲህ አለው እናንተ የይሁዳና የብንያም ሰዎች እግዚአብሔርን ፈልጉ ከእርሱ ጋር ሁኑ ከእናንተ ጋርም ይሆናል ብትተውት ይተዋችኃል ብትፈልጉትም ይገኝላቸዋል።
እስራኤልም ብዙ ዘመን ያለ እውነተኛ አምላክ ያለ አስተማሪም ካህን፣ ያለ ሕግ ይኖሩ ነበር
በመከራቸው ግዜ ወደ እስራኤል አምላክ ወደ እግዚአብሔር ተመልሰው በፈለጉት ግዜ አገኙት!
እስራኤል እግዚአብሔርን ባልፈለጉበት ግዜ ለብዙ መከራና ድንጋጤ ለመጨነቅና ሰላም ለማጣት ወገን ከወገን ከተማ ከከተማ ጋር ጦርነት ተላልፈው እንደተሰጡና እንደተዳረጉ እናንተም እንደ እነሱ እንዳትሆኑ እግዚአብሔርን ፈልጉ ለመልካም ሥራችሁ ብድራት አላችሁና ፍለጋችሁን ቀጥሉ በርቱ እጃችሁ አይላላ ብሎ በመንፈስ ሆኖ ብዙ መከራቸው አበረታታቸው እነሱም አሳና ሕዝቡ ሰሙ ለመጣላቸው ትንቢታዊ ድምፅ አዎንታዊ ምላሽ ሰጡ ፀያፉን ነገር ሁሉ ከከተማቸው አስወገዱ በእግዚአብሔር ቤት የነበረውን የእግዚአብሔርን መሠዊያ አደሱ መስዋት አቀረቡ።
ሕዝቡም ሁሉ ተሰብስበው እግዚአብሔርን ይፈልጉ ዘንድ ቃል ኪዳን አደረጉ አዋጅም አወጡ እግዚአብሔርን የማይፈልግ ሰው ይገደል የሚል ነበር ንጉሡ አሳ እናቱ መዓካ ጣኦት ተክላ የማምለኪያ አፀድ ስለሰራች ከእቴጌነቷ ክብር አወረዳት ጣኦቱንም ቀጥቅጦ አቃጠለው።
እግዚአብሔርም በምላሹ ተገኘላቸው በዙሪያቸው እረፍት ሰጣቸው። እግዚአብሔርን ከልብ ፈለጉት፤ እርሱም ተገኘላቸው፤ ስለዚህ እግዚአብሔር በሁሉም አቅጣጫ ዕረፍት ሰጣቸው። (2 ዜና መዋዕል 15:15)
.. የአሳ ልብ በዘመኑ ሁሉ ፈጽሞ ለእግዚአብሔር የተገዛ ነበር። (2 ዜና መዋዕል 15:17-18)
እግዚአብሔርም በምላሹ ከሰልፍና ከጦርነት ነፃ አደረገው አሳረፈው፤ እስከ ሠላሳ አምስተኛው የአሳ ዘመነ መንግሥት ድረስ ምንም ዐይነት ጦርነት አልነበረም። (2 ዜና መዋዕል 15:19)
ከዚህ የምንማራቸው መርሆች፦
መርህ 1፦ አገልጋዮች ልክ እንደ ነብዩ ዓዛርያስ ሕዝቡ ከልብ እግዚአብሔርን እንዲፈለጉ ጥሪ እንዳደረገና እንደመለሰ ትንቢታዊ ጥሪ እንድናደርግና በተለይ በዚህ ግዜ ትውልዱ ነፍሱ በተራቆተችበትና ተቅበዝባዥ በሆነበት ግዜ እንዲያርፍ ብቸኛው መንገድ እግዚአብሔርን መራብና መፈለግ ስለሆነ አበክረን ልናስተምርና ልንመልሰው ይገባል።
በማስታገሻ ቤተክርስቲያን ሳሚ ብቻ አናድርገው ትውልድ ታሟል ይፈወስ ታመናል እንፈወስ መንፈሳዊ ረሃብ ከሌለን መንፈሳዊ ሕመም ታመናልና እግዚአብሔር ይፈውሰን።
መርህ 2፦ መሪዎችና ሕዝቡ እግዚአብሔርን ለመፈለግ ልንሰበሰብ ልንወስን ልንጨክን ፀያፍ የሆነውን ነገር ከሕይወታችን ልናስወግድ ይገባል።
መርህ 3፦ ወደ እግዚአብሔር ቤት ልንሮጥና መሰዊያችንን(ሕብረታችንን፣ ፀሎታችንን አምልኮአችንን) ልናድስ ይገባል።
መርህ 4፦ አሳ በዘመኑ ሁሉ ለእግዚአብሔር እንደተሰጠ እኛም በዘመናችን ሁሉ ልንሰጥ ይገባል።
እነዚህን መርሆዎች መከተል ደግሞ የሚያመጡት ውጤት አለ።
እግዚአብሔር በሁሉም አቅጣጫ ዕረፍት እንደሰጣቸው ለእኛም በሁሉም አቅጣጫ እረፍት ይሆንልናል። አሜን!
ፀሎት
“አንተ ፊቴን ፈልጉ” ባልህ ጊዜ፤
ልቤ እግዚአብሔር ሆይ፤ ፊትህን እሻለሁ አለች። (መዝሙር 27:8)
አቤቱ አምላኬ እግዚአብሔር ሆይ አንተን የሚራቡበትን የሚፈልጉበትን መንፈሳዊ ረሃብ እንድተሰጣቸው ለአንተ ፍላጎት(ሃፒታይት) ካሳጣቸው መንፈሳዊ በሽታ በኢየሱስ ሥም ይፈወሱ! አሜን
በአገልጋይ ጌትነት አለሙ
ኤፍታሕ የሕያው እግዚአብሔር ቤ/ክ
በእግዚአብሔር ቤት መሆን
#ክርስቲያን #ኢየሱስ #አምልኮ #ስብከት #ቃል #ፕሮቴስታንት #ፕሮቴስታንትመዝሙር #መዝሙር #ጴንጤ #ኢየሱስ #አምልኮ #መዝሙር #
15/05/2026
ድንቅ ትምህርት በወንድም ቤኪ
በኢያኢሮስ መንገድ ላይ | አገልጋይ ቤኪ| ኤፍታህ ቤተክርስቲያን | ትምህርት | ECLG Church | #2026 ኤፍታህ የሕያው እግዚአብሔር ቤተክርስቲያንአድራሻ፦ አዲስ አበባ ፤ ቦሌ አራብሳEPHPHATHA CHURCH OF THE LIVING GODAddis Ababa, Ethiopia.Phone Number:- ☎️ +251952013404 ...
11/05/2026
የታረደው በግ ይገባዋል
ራዕይ 5፡1–14
መግቢያ
የራዕይ መጽሐፍ የተጻፈው ሐዋርያው ዮሐንስ በፍጥሞ ደሴት በግዞት እያለ ነው። ምዕራፍ 4 የእግዚአብሔርን ዙፋን እና ሰማያዊ አምልኮን ይገልጣል። ምዕራፍ 5 ራእዩን ይቀጥላል ነገር ግን አንድ ትልቅ ቀውስ ያስተዋውቃል፡- በእግዚአብሔር እጅ ጥቅልል አለ፣ ነገር ግን ማንም ሊከፍተው የሚገባው ሆኖ አልተገኘም።
1. በእግዚአብሔር እጅ ያለው ጥቅልል (ራእይ 5፡1–4)
የጥቅልሉ ትርጉም፡-
* የእግዚአብሔርን መለኮታዊ ዕቅድ እና ዓላማዎች ይወክላል።
* ፍርድን፣ ቤዛነትን እና የታሪክን ፍጻሜ ይዟል።
2. በግ የሆነው አንበሳ (ራዕይ 5፡5–7)
እርሱም፡-
* በኃይሉ እንደ አንበሳ
* በመሥዋዕትነት እንደ በግ ተጠቅሷል
3. ኢየሱስ የሚገባው ለምንድን ነው (ራዕይ 5፡8–10)
ሀ. ስለ ታረደ
ብቃቱ ከመሥዋዕትነቱ ጋር የተሳሰረ ነው።
ክርስትና በክርስቶስ የስርየት ሞት ላይ ያተኮረ ነው።
ለ. ለእግዚአብሔር ሰዎችን ስለዋጀ(ስለገዛ)
9 "...ታርደሃልና፥ በደምህም ለእግዚአብሔር ከነገድ ሁሉ ከቋንቋም ሁሉ ከወገንም ሁሉ ከሕዝብም ሁሉ ሰዎችን ዋጅተህ ለአምላካችን መንግሥትና ካህናት ይሆኑ ዘንድ አደረግሃቸው፥ "
ሐ. መንግሥትና ካህናት ስላደረጋቸው
አማኞች ይቅር የሚባሉት ብቻ አይደሉም፤ ማንነትና ጥሪ ተሰጥቷቸዋል።
* መንግሥት (የእግዚአብሔር መንግሥት የሆነ)
* ካህናት (ወደ እግዚአብሔር መድረስና ለሌሎች አገልግሎት መስጠት)
4. የፍጥረት ሁሉ አምልኮ (ራእይ 5:11–14)
ዮሐንስ በእልፍ የሚቆጠሩ መላእክት እንዲህ ሲሉ ሰምቷል፡-
“በጉ የሚገባው ነው…” ምን ??
* ኃይል
* ባለ ጠግነት
* ጥበብ
* ብርታት
* ክብር
* ምስጋና
* በርከት
ክርስቶስ ሙሉ አምልኮ ይገባዋል።
እውነተኛ መገለጥ ወደ እውነተኛ አምልኮ ይመራል።
ከራእይ ምዕራፍ 5 ቁልፍ ትምህርቶች
1. ኢየሱስ ብቻ የሚገባው ነው
መሪዎች፣ ሀብት፣ ስኬቶች ወይም ሃይማኖት አይደሉም።
ክርስቶስ ብቻ ነው እውነተኛ አምልኮ የሚገባው።
2. መስቀል ለድል ማዕከላዊ ነው
ዓለም የመስቀሉን ስራ ለማጥፋት በተከያየ ስሁት ሀሳብ ይተጋል።
ፍጥረት የመሥዋዕትነት ፍቅሩን ከፍ አድርጎ ይቀኛል
3. አምልኮ ለቤዛነት ትክክለኛው ምላሽ ነው
ክርስቶስ ያደረገውን ሲረዱ፣ አምልኮ ተፈጥሯዊ ይሆናል።
4. ታሪክ በእግዚአብሔር እጅ ውስጥ ነው
በፓስተር ቶማስ ሰብስቤ
የእሁድ የአምልኮ ግዜ
አጋፔ ከዚህ ዓለም ፍቅር የሚለየው....
#ክርስቲያን #ኢየሱስ #ፍቅር #ፕሮቴስታንት
04/05/2026
እግዚአብሔር ያስቀጥላችኃል !!!
ፊሊ 1:3-11
“በእናንተ መልካምን ሥራ የጀመረው እስከ ኢየሱስ ክርስቶስ ቀን ድረስ እንዲፈጽመው ይህን ተረድቼአለሁና፤”
— ፊልጵስዩስ 1፥6
የፊልጵስዩስ መፅሐፍ ሐዋርያው ጳውሎስ በተደጋጋሚ ስለ ላኩለት ስጦታ(ፊል 4:18) ለማመስገን የፃፈላቸው መልዕክት ሲሆን በውስጡ ግን ስለ ደስታ፣ ስለ ትህትና፣ ስለ ክርስቶስ አምላክነት እና መመሪያዎችንና ፀሎቶችን የያዘ አስደናቂ መፅሐፍ ነው።
የፊሊጵስዩስ ሰዎች እነ ጳውሎስ በሐዋርያት ሥራ 16፥6 -15 ወደ እስያ እንዳይሔዱ በመንፈስ ቅዱስ ከተከለከሉ በኋላ አውሮፓ ወደ መቄዶንያ አገር ወደ ፊልጵስዩስ ከተማ በራዕይ ተረድተው ወንጌልን ከሰብከውላቸው በኋላ ነው ወደ እግዚአብሔር መንግስት የተጨመሩ ናቸው።
ጳውሎስ የፊሊጵስዩስ ሰዎችን እያሰበ አምላኬን አመሰግናለሁ ይላል፣ ስለእነርሱ በደስታ ይፀልያል እስከ ፍፃሜው እንደሚቀጥሉ እርግጠኛ ነኝ ይላል።
ምክንያቱም በእነርሱ መልካም ስራ የጀመረው እራሱ እግዚአብሔር ስለሆነ ስለመቀጠላቸው እርግጠኛ ይሆናል እንዲሁም በፅድቅ ፍሬ እንዲሞሉ ፣ የእግዚአብሔር ፍቅር በዕውቀትና በማስተዋል እያደገ እንዲበዛ ይፀልይላቸዋል።
ከዚህ የመጽሐፍ ቅዱስ ክፍል 4 መርሆችን እንማራለን።
መርህ 1
ያስጀመራችሁ እግዚአብሔር ከሆነ በምንም ሁኔታ ሁኑ ትቀጥላላችሁ!
መርህ 2
ራስን ለጌታም ለወንጌልም መስጠት እንደሚገባ።
“አስቀድመውም በእግዚአብሔር ፈቃድ ራሳቸውን ለጌታ ለእኛም ሰጡ እንጂ እንዳሰብን አይደለም።”
— 2ኛ ቆሮ 8፥5
መርህ 3
ፍፃሜንና ተስፋን መስጠት የሚችለው እግዚአብሔር ብቻ እንደሆነ ተረድተን በእግዚአብሔር ብቻ መደገፍ እንዳለብን።
“ለእናንተ የማስባትን አሳብ እኔ አውቃለሁ፤ ፍጻሜና ተስፋ እሰጣችሁ ዘንድ የሰላም አሳብ ነው እንጂ የክፉ ነገር አይደለም።”
— ኤርምያስ 29፥11
መርህ 4
እንደምንደርስ እርግጠኛ ብንሆንም መፀለይን መቀጠል አለብን።
“ለእግዚአብሔርም ክብርና ምስጋና ከኢየሱስ ክርስቶስ የሚገኝ የጽድቅ ፍሬ ሞልቶባችሁ፥ ለክርስቶስ ቀን ተዘጋጅታችሁ ቅኖችና አለ ነውር እንድትሆኑ የሚሻለውን ነገር ፈትናችሁ ትወዱ ዘንድ፥ ፍቅራችሁ በእውቀትና በማስተዋል ሁሉ ከፊት ይልቅ እያደገ እንዲበዛ ይህን እጸልያለሁ።”
— ፊልጵስዩስ 1፥9-11
በወንድም አሴር ሊሻን
25/8/2018 ዓ.ም
ኤፍታህ የሕያው እግዚአብሔር ቤተክርስቲያን
02/05/2026
መጽሐፍ ቅዱስን የማንበብ ፍላጎት ማጣት የመንፈሳዊ ሕይወት መታመም ምልክት ነው።
የምግብ ፍላጎት መቀነስ የበሽታ አንዱ ምልክት እንደሆነ ሁሉ ለእግዚአብሔርን ቃል ያለን ረሀብ መቀነስ በመንፈሳዊ ህይወት መታመም ምልክት ነው።
ምግብን መመገብ ረሀብን ከማስታገስ ባለፈ የተጎዳ አካልን ለመጠገን፡ አካልን ለማጠንከር፡ እድገትን ለማስቀጠል፡ አይምሮን ለማጠንከር፡ ጤናን ለመጠበቅ፡ ከዚያም ባለፈ በአጠቃላይ፡በሕይወት ለመቆየት ወሳኝ ነገር ነው።
ከዚህ በተሳሳይ ታዲያ በመንፈሳዊ ሕይወታችን ለማሳደግ፡ ጠንካራ ለመሆን፡ ጤናማ ኑሮ እንዲኖረን፡ በአጠቃላይ ለመንፈሳዊ ሕይወታችን መቀጠል ወሳኝ ነው።
በክርስትና ህይወት ለማደግ ደግሞ የእግዚአብሔርን ቃል መመገብ አማራጭ የሌለው ጉዳይ ነው።
ለዚህም ነው ሐዋርያው ቅዱስ ጴጥሮስ በመጀመሪያው መልዕክቱ ምዕራፍ 2፥1-3 የቃሉን ወተት እንደ አዲስ ህጻን እንድንፈልገው የሚነግረን።
በዛሬው ዕለት ኤፍታሕ የሕያው እግዚአብሔር ቤተክርስቲያን የቤት ኅብረት የቃል ጥናት ተጀምሯል።
በዚህ ፕሮግራም ላይ የእግዚአብሔር ቃል ጥናት የተጀመረ ሲሆን መጥታችሁ በጸሎት ቃል በማጥናት ከእኛ ጋር ሕብረት እንድታደርጉ ተጋብዛችኋል።
28/04/2026
የሐዋርያት ስራ ምዕራፍ 2
¯¯¯¯¯¯¯¯¯¯
¹ በዓለ ኀምሳ የተባለውም ቀን በደረሰ ጊዜ፥ ሁሉም በአንድ ልብ ሆነው አብረው ሳሉ፥
² ድንገት እንደሚነጥቅ ዓውሎ ነፋስ ከሰማይ ድምፅ መጣ፥ ተቀምጠው የነበሩበትንም ቤት ሁሉ ሞላው።
³ እንደ እሳትም የተከፋፈሉ ልሳኖች ታዩአቸው፤ በያንዳንዳቸውም ላይ ተቀመጡባቸው።
⁴ በሁሉም መንፈስ ቅዱስ ሞላባቸው፥ መንፈስም ይናገሩ ዘንድ እንደ ሰጣቸው በሌላ ልሳኖች ይናገሩ ጀመር።
⁵ ከሰማይም በታች ካሉ ሕዝብ ሁሉ በጸሎት የተጉ አይሁድ በኢየሩሳሌም ይኖሩ ነበር፤
⁶ ይህም ድምፅ በሆነ ጊዜ ሕዝብ ሁሉ ተሰበሰቡ፥ እያንዳንዱም በገዛ ቋንቋው ሲናገሩ ይሰማ ስለ ነበር የሚሉትን አጡ።
Click here to claim your Sponsored Listing.
Category
Contact the place of worship
Telephone
Website
Address
Bole Ararsa
Addis Ababa