Ethio Color Media
Ethio Color Media
ኢትዮጵያዬ ቀለም!
17/09/2022
ከአዲስ አበባ ጎዳናዎች የተነሱ 1,897 ዜጎች በፍላጎታቸው ወደየመጡበት አካባቢ ተሸኙ
የአዲስ አበባ ሴቶች፣ ህፃናትና ማህበራዊ ጉዳይ ቢሮ ውሎና አዳራቸውን ጎዳና ላይ ያደረጉ ዜጎችን ከጎዳና ላይ በማንሳት የህይወት ክህሎት ስልጠና በመስጠት 1,615 ወንዶች እና 282ሴቶችን በአጠቃላይ 1,897 ዜጎችን በፍላጎታቸው መሰረት ወደመጡበት በሰሜን፣ ደቡብ፣ ምስራቅና ምዕራብ አቅጣጫዎች በዛሬው ዕለት ሽኝት አድርጓል።
ቢሮው በ2015 በጀት ዓመት በመጀመሪያ ዙር 3,273 ዜጎችን ከጎዳና ላይ ያነሳ ሲሆን ዛሬ 1,897 በፍላጎታቸው መሰረት ወደ በቤተሰባቸው ተሸኝቷል።
ቀሪዎቹ 1,376 ከጎዳና የተነሱ ሰዎች ወደስራ ለማሰማራትና ተደራራቢ የአካልጉዳት ያለባቸውንና ዕድሜያቸው የገፉ አረጋውያንን ዘላቂ የተቋም አገልግሎት እንዲያገኙ እየተሰራ መሆኑ ተጠቁሟል።
Ethio Color Media
15/08/2022
What a Gol! Abubekir Nasir - አቡበክር ናስር
12/08/2022
Grand Ethiopian Renaissance Dam (GERD)
Ethiopia completes third GERD filling|የግድቡ 3ኛ ዙር የውሃ ሙሌት ተጠናቀቀ (GERD)
Ethiopia completes third GERD filling
The third filling of the Grand Ethiopian Renaissance Dam (GERD) has been completed, according to the Ethiopian Electric Power (EEP).
The announcement was made just one day after the second turbine of the dam became operational, adding 375 mw of electricity to the national grid. EEP said the water is now flowing above the reservoir.
Grand Ethiopian Renaissance Dam
11/08/2022
የታላቁ ኢትዮጵያ ሕዳሴ ግድብ ሁለተኛው ተርባይን የኤሌክትሪክ ኃይል ማመንጨት ጀምሯል
እንኳን ደስ አለን!!
Ethio Color Media
05/08/2022
የቴሌ ብር ፋይናንስ አገልግሎት አዳዲስ አገልግሎቶችን ይፋ አደረገ
የኢትዮ ቴሌኮም አካል የሆነው የቴሌ ብር ፋይናንስ አገልግሎት በዛሬው እለት ቴሌ ብር እንደኪስሴ፣ ቴሌ ብር መላና ቴሌ ብር ሳንዱቅ የተሰኙ አገልግሎቶችን ይፋ አደርጓል።
ቴሌ ብር እንደኪሴ አገልግሎት የቴሌ ብር ደንበኞች ያላቸው ቀሪ ሂሳብ መጠን በቂ ባልሆነበት ጊዜ የብድር አገልግሎት እንዲያገኙ የሚያስችል ነው። ቴሌ ብር መላ ለግለሰብ እና ለነጋዴዎች ቢዝነስ እንዲጀምሩ ወይም እንዳስፋፉ በኤሌክትሪክ ገንዘብ አነስተኛ መጠን ያለው ብድር የሚያገኙበት አገልግሎት ነው። ሦሥተኛው አገልግሎት ቴሌ ብር ሳዱቅ ወይም ቁጠባ ሲሆን፣ ደንበኞች በተሻለ ወለድ ወይም ከወለድ ነጻ የሚቆጥቡበት አገልግሎት ነው።
ኢትዮ ቴሌኮም አገልግሎቱን ይፋ ያደረገው ከዳሸን ባንክ ጋር በመተባበር ነው። ቴሌ ብር እስካሁን የገንዘብ ዝውውሮችንና የአገልግሎት ክፍያዎችን ለመክፈል ሲሆን፣ 22.2,ሚሊዮን ደንበኞችን አፍርቶ 34.1 ቢሊዮን ብር ዝውውር ማድረጉን የኢትዮ ቴሌኮም ሥራ አሰፈጻሚ ፍሬሕይወት ታምሩ ጠቁመዋል።
Ethio Color Media
05/08/2022
መቀሌ ደርሰው የተመለሱ ልዩ መልዕክተኛች ሁኔታውን እንዳላስደሰተው መንግስት አስታወቀ
በአሜሪካ የምስራቅ አፍሪካ ልዩ መልእክተኛ ማይክ ሀመር የተመራው የመልዕክተኞች እና የአምባሳደሮች ልዑክ የመቀለ ቆይታ ከሰላም ንግግር ይልቅ በህወሀት በተቀመጡ ቅድመ ሁኔታዎች ላይ ያተኮረ እንደነበር አምባሳደር ሬድዋን ሁሴን በትዊተር ገፃቸው ገለፀዋል።
እርግጥ የሆነ የሰላም ንግግር እንዲጀመር ከማድረግ አንፃር ተጨባጭ ነገር አላመጡም ያሉት አምባሳደሩ ይልቁንም የመልእክተኞቹ እና የአምባሳደሮቹ ቡድን በህወሓት የተቀመጡ ቅድመ ሁኔታዎችን ማሟላት ላይ አተኩሯል በማለት ገልፀዋል።
የተቋረጡ አገልግሎቶችን ከመመለስ አኳያ መንግስት ዝግጁ መሆኑን ያነሱት አምባሳደሩ ለዚህ መሳካት የጎደለው ነገር መሟላት እንዳለበት በመግለፅ የጎደለው ሁኔታዎቹን ማመቻቸትና ሰላምን በንግግር መጀመር እንደሚያስፈልግ አስምረውበታል።
የዲፕሎማቶቹ ቡድን የጋራ መግለጫ "ያልተገደበ የሰብአዊ እርዳታ" ጉዳይን አሁንም በድጋሜ ማንሳቱን በመግለፅ መንግስት ጥያቄው ቀድሞ የመለሰው መሆኑን ጠቁመዋል።
አምባሳደር ሬድዋን ወደ መቀለ የሚደረጉ በረራዎች ላይ ምንም አይነት ገደብ የለም ካሉ በኋላ እርዳታ የጫኑ ተሽከርካሪዎችም እንዲሁ ክልከላ የለባቸውም ብለዋል። የነዳጅ ጉዳይ በተመሳሳይ መልስ ማግኝቱን ግልፀዋል።
የአፍሪካ ህብረት ብቸኛው የንግግር መንገድ እንደሆነ አምባሳደሩ በመልዕክታቸው አረጋግጠዋል።
Ethio Color Media
Ethio Color Media
ኢትዮጵያዬ ቀለም!
Click here to claim your Sponsored Listing.
Category
Contact the business
Website
Address
Arat Kilo
Addis Ababa
12/08/2022
02/08/2022
02/08/2022