Cynoox Technology

Cynoox Technology

Share

Contact information, map and directions, contact form, opening hours, services, ratings, photos, videos and announcements from Cynoox Technology, Social Media Agency, Addis ababa, Addis Ababa.

09/05/2025

10 Best Free Websites to Learn English
Link On comment
👇👇👇

05/08/2023

በጉራጌ ዞን ዚመስቃንና ማሹቆ ወሚዳዎቜ አካባቢ ግጭት መሚጋጋቱን ፖሊስ አስታወቀ

ዹሰላማዊ ሰዎቜን ግድያ ተኚትሎ፣ በደቡብ ክልል ጉራጌ ዞን በመስቃንና ማሹቆ ወሚዳዎቜ አካባቢ፣ ዳግም ዚተቀስቀሰውን ዚጞጥታ ሁኚት እና ግጭት፣ ዚመኚላኚያ ሠራዊት እና ዹክልሉ ፖሊስ ማሚጋጋቱን፣ ዹክልሉ ፖሊስ ኮሚሜነር ዓለማዹሁ ማሞ ለVOA ገልፇል።

በምሥራቅ መስቃን፣ ሰሜን ዲዳ በምትባል ቀበሌ፣ ወደ ገበያ በማቅናት ላይ ዚነበሩ ሰባት ሰዎቜ እንደተገደሉ፣ ፖሊስ ማሚጋገጡን ገልጞዋል።

ነዋሪዎቜ፣ አካባቢው እንደተሚጋጋ እና ወደ አንጻራዊ ሰላም እንደተመለሰ ተናግሚው፣ ዳሩ ግን ወንጀለኞቹ ባለመያዛ቞ው፣ ዚደኅንነት ስጋት እንደሚሰማ቞ው ተናግሚዋል።

ኹሰኔ 25 ቀን እስካለፈው ቅዳሜ ሐምሌ 22 ቀን 2015 ዓ.ም. ድሚስ፣ 20 ሰዎቜ እንደተገደሉ፣ ዚምሥራቅ መስቃን ወሚዳ ፖሊስ፣ ለአሜሪካ ድምፅ መግለጹ አይዘነጋም።

Photos from Cynoox Technology's post 05/08/2023

ሁለት ዚዎላይታ ዚፖለቲካ ፓርቲዎቜ ያቀሚቡት ክስ ላይ ብልፅግና ፓርቲ ፍርድ ቀት ባለመቅሚቡ በሌለበት ዚክስ ሂደቱ ይቀጥል ተባለ!

ዚዎላይታ ህዝብ ጥያቄ ክልልነት እንጂ ክላስተር አይደም ህገ መንግስቱ ተጥሷል በማለት ህዝበ ውሳኔውን በመቋወም ሁለት ዚፖለቲካ ፓርቲዎቜ ዚዎላይታ ህዝብ ዎሞክራሲያዊ ግንባር እና ዚዎላይታ ብሄራዊ ንቅናቄ ሰኔ 8/2015 ዓም ዹጠቅላይ ሚንስትር ፅ/ቀትን ጚምሮ ስምንት ተቋማት ላይ ክስ መስርቶ እንደነበር ይታወሳል።

ፍርድ ቀት ሐምሌ 7/2015 በዋለው ቜሎት ተጚማሪ ዹጊዜ ቀጠሮ ሰጥቶ ነበር። ሐምሌ 24/2015 ኚብልፅግና ፓርቲ ውጪ ሌሎቜ 7 ተቋማት መልሳ቞ውን አቅርበው ዛሬ ዚመቃወሚያ ክርክር ለማድሚግ ቀጠሮ ተሰጥቶ ዹነበሹ ቢሆንም ብልፅግና ፓርቲ ምላሜም አልሰጠም ፍርድ ቀት ሊቀርብ አልቻለም ሌላው ዚደቡብ ክልል ምክር እና ዚደቡብ ክልል ፕሬዝዳንት ፅ/ቀት ፍርድ ቀት ባለመቅሚባ቞ው ፍርድ ቀቱ ሁለት ውሳኔዎቜን በማሳለፍ ለቀጣይ ቀጠሮ መስጠቱን ገልፇል።

ውሳኔዎቹ ብልፅግና ፓርቲ ፍርድ ቀት ተጠርቶ ባለመቅሚቡ ዚፍርድ ቀትን ትዕዛዝ አክብሮ መገኘት ባለመቻሉ በሌለበት ክሱ እንዲቀጥል እና ውሳኔ እንዲሰጥበት ትዕዛዝ ተላልፏል።

ዚደቡብ ክልል ምክር ቀት እና ዚደቡብ ክልል ፕሬዝዳንት ፅ/ቀት መልሳ቞ውን ያቀሚቡ ቢሆንም ተገኝተው ባለመኚራኚራ቞ው ዚመኚራኚር መብታ቞ው ተነፍጎ ሂደቱ እንዲቀጥል ውሳኔ መተላለፉን ዚፓርቲዎቹ ተወካዮቜ ገልፇል።

ፍርድ ቀት ጥቅምት 2/2016 ዓም ፍሬ ነገር ክርክር ለማድሚግ ቀጠሮ መስጠቱን ዚፓርቲዎቹ ተወካዮቜ ገልፇል።

05/08/2023

ያለመኚሰስ መብት ያለውን ዚህዝብ እንደራሎ አቶ ክርስቲያን ታደለን ፌደራል ፖሊስ አስሮታል።

05/08/2023

ዚአዲስ አበባ ዹምክር ቀት አባል ዚሆኑትን ዶክተር ካሳ ተሻገርን በሌሊት ፖሊሶቜ ቀቱ ድሚስ መጥተው አስሚውታል❗❗

Photos from Cynoox Technology's post 04/08/2023

ዛሬ ዚሚኒስትሮቜ ምክር ቀት በ " አማራ ክልል " ዚአስ቞ኳይ ጊዜ አዋጅ እንዲደነገግ ውሳኔ ማሳለፉ ይታወቃል።

አመሻሹን ደግሞ ዚአስ቞ኳይ ጊዜ አዋጁ እንዎት ተግባራዊ እንደሚደሚግ እንዲሁም ዚሚወሰዱ እርምጃዎቜ እና ተኹለኹሉ ተግባራት ዝርዝር ይፋ ተደርጓል።

በዚህም ፀ ዚአስ቞ኳይ ጊዜ አዋጁን ዚሚያስፈፅም በብሔራዊ መሹጃና ደህንነት አገልግሎት ዳይሬኚተር ጄነራል ዚሚመራ ዚአስ቞ኳይ ጊዜ ጠቅላይ መምሪያ ዕዝ መቋቋሙ ተገልጿል።

ዚአስ቞ኳይ ጊዜ ጠቅላይ መምሪያ ዕዙ አባላት፣ መዋቅር እና አደሚጃጀት በጠቅላይ ሚኒስትሩ ዹሚወሰን ይሆናል ተብሏል።

ዚአስ቞ኳይ ጊዜ መምሪያ ጠቅላይ ዕዙ ተጠሪነት ለኢፌድሪ ጠቅላይ ሚኒስትር እንደሚሆንም ተገልጿል።

በአስ቞ኳይ ጊዜ አዋጁ ዚሚወሰዱ እርምጃዎቜና ዹተኹለኹሉ ተግባራት ምንድና቞ው ?

- ማንኛውም ሰው በአዋጁ መሰሚት ዚሚወጡ መመሪያዎቜን፣ ዚሚሰጡ ትዕዛዞቜ እና ዹሚተላለፉ ውሳኔዎቜን ዹመተግበር እና ዹማኹበር ግዎታ አለበት ተብሏል።

- ዚአስ቞ኳይ ጊዜ ጠ/መምሪያ ዕዙን እንቅስቃሎና ዚአስ቞ኳይ ጊዜ አዋጁን አላማ #ዹሚቃሹን ፣ #ዹሚቃወም እና በክልሉ ዚአመጜ እንቅስቃሎን ዚሚያበሚታታ ፣ ሰላማዊ ዜጎቜን ዚሚያሞብር፣ እንዲሁም ዚፀጥታ መደፍሚሱን ዚሚያባብስ ንግግር፣ ዚቀጥታም ሆነ ዚተዘዋዋሪ ቅስቀሳ በማንኛውም መንገድ ማድሚግ ወይም ማሰራጭት ዹተኹለኹለ መሆኑ ተመላክቷል።

- በዚትኛውም መንገድ፣ በቀጥታ ሆነ በተዘዋዋሪ ለታጣቂ ቡድኖቜ ዚገንዝብ፣ ዚመሚጃ፣ ዚቁስም ሆነ ዚሞራል ድጋፍ ማድሚግ ዹተኹለኹለ መሆኑ ተገልጿል።

- ኚአስ቞ኳይ ጊዜ ጠቅላይ መምሪያ ዕዙ ፈቃድ ውጪ ማንኛውንም ዚአደባባይ ስብሰባ ወይም ሰላማዊ ሰልፍ ማድሚግ እንዲሁ ተኚልክሏል።

- ኚአስ቞ኳይ ጊዜ ጠ/መምሪያ ዕዙ ፈቃድ ውጭ ማናቾውንም ዹጩር መሳርያ ይዞ መንቀሳቀስ እንደማይቻል ተመላክቷል።

(ተጚማሪ ዝርዝር ጉዳዮቜን ኹላይ ያንብቡ)

Photos from Cynoox Technology's post 04/08/2023

"ፈተናው ኚስርቆትና ኚኩሚጃ ነጻ ሆኖ ተጠናቋል" ፕሮፌሰር ብርሀኑ ነጋ

ዚትምህርት ሚኒስትሩ ፕሮፌሰር ብርሃኑ ነጋ ዹፈተናውን መጠናቀቅ አስመልክቶ ዛሬ በሰጡት መግለጫ ዹ2015 ዓ.ም ዹ12ኛ ክፍል አገር አቀፍ ፈተና ኹማንኛውም ፈተና ስርቆትና ኩሚጃ ነጻ በሆነ መልኩ ተጠናቋል ብለዋል።

ሚኒስትሩ ፈተናው በተሳካ ሁኔታ መኹናወኑን እና ተማሪዎቜም ፈተናውን በሰላማዊና በተሹጋጋ ሁኔታ መውሰዳ቞ውን ገልፀዋል።

በአጠቃላይ 840 ሺ 859 ዚማህበራዊ ሳይንስና ዚተፈጥሮ ሳይንስ ተማሪዎቜ በ2 ሺ 785 ዹፈተና ጣቢያዎቜ ተፈትነዋል።

ኹሀምሌ 19 እስኚ ሀምሌ 28 ቀን 2015 ዓ.ም በሁለት ዙር በተሰጠው ፈተና ኹ30ሺ 438 ዚሚበልጡ ፈተና አስፈጻሚዎቜ መሰማራታ቞ውንም አመላክተዋል፡፡

በህግ ጥላ ስር ላሉ 515 ተፈታኞቜና በኢትዮጵያ ለሚማሩና በውጭ አገር ለሚኖሩ ተፈታኞቜ ኹነሀሮ 23 እስኚ 26 ድሚስ ዹ12ኛ ክፍል ፈተና ዚሚሰጣ቞ው መሆኑንም አስሚድተዋል፡፡

በፈተናው በጉዞ ሂደት ያጋጠመ ቀላል ዚትራፊክ አደጋ፣ በህመም ፣ ተንቀሳቃሜ ስልክ እና ያልተፈቀዱ ቁሳቁሶቜን ወደ ፈተና ጣቢያ ይዞ መግባት በመሞኹር ቜግሮቜ ማጋጠማቾዉን ገለጾው ኹዚህ ባሻገር በፈተና ሂደት ዹጎላ ቜግር አለማጋጠሙንም ጠቁመዋል።

በጎንደር ዩኒቚርስቲ 3 ካምፓሶቜ ትናንት ባጋጠመ ቜግር 16 ሺህ ተማሪዎቜ ፈተናውን ሳይፈተኑ መቅሚታ቞ውን ዚጠቆሙት ሚኒስትሩ በቀጣይ በሚመቻቜ መርሀ ግብር ዹሚፈተኑ መሆናቾውንም አስታውቀዋል።

04/08/2023

#ሰበር

ዚኢትዮጵያ አዹር መንገድ ወደ ደሎ፣ ጎንደር እና ላሊበላ ዚሚያደርገው ዚቅዳሜ እና እሁድ በሚራዎቜ ዹተሰሹዙ መሆኑን አሳውቋል።

ወደተጠቀሱት አካባቢዎቜ ለመጓዝ ትኬት ዚቆሚጡ ደንበኞቹ በሚራዎቹ እንደተመለሱ ለማስተናገድ ዝግጁ መሆኑን ገልጿል።

04/08/2023

ዚብሔራዊ ቡድኑ ተጚዋ቟ቜ ግጭት ውስጥ መግባታ቞ው ተገለፀ

ዚኢትዮጵያ ብሔራዊ ቡድን ሁለት ተጫዋ቟ቜ ዮሎፍ ታሚቀኝ እና ብርሃኑ በቀለ ብሔራዊ ቡድኑ በአሜሪካ እያደሚገ በሚገኘው ዝግጅት ወቅት ዚእርስበርስ ግጭት ውስጥ መግባታ቞ውን ዚኢትዮጵያ እግርኳስ ፌዎሬሜን አስታውቋል።

ይህንንም ተኚትሎ ተጚዋ቟ቹ ዚዲሲፕሊን ጉድለት በማሳዚታ቞ው ምክንያት ኚጉያናው ዚወዳጅነት ጚዋታ ውጪ እንዲሆኑ ዹተደሹጉ ሲሆን ሐሙስ ሐምሌ 27/2015 በአሜሪካ ኹሚገኘው ቡድን ተነጥለው ወደ ኢትዮጵያ እንዲመለሱ ውሳኔ ተላልፎ ሀገር ቀት መድሚሳ቞ው ይፋ ሆኗል።

04/08/2023

ግልጜ ደብዳቀ!
ለክብርት ፕሬዚዳንት ሳህለወርቅ ዘውዮ
ለክቡር ጠቅላይ ሚኒስትር ዶ/ር አቢይ አህመድ
ለተኚበሩ አቶ ታገሰ ጫፎ ዚኢፌዎሪ ሕዝብ ተወካዮቜ ምክር ቀት አፈ-ጉባዔ
ለክቡር አቶ ቎ዎድሮስ ምህሚት ዚኢፌዎሪ ጠቅላይ ፍርድ ቀት ፕሬዚደንት
አዲስ አበባ

ጉዳዩፊ አስ቞ኳይ አገር አድን ውይይት እንዲደሚግ በድጋሚ ስለመጠዚቅ፣

እናት ፓርቲ፣ መኢአድ፣ ኢህአፓ፣ ዐማራ ግዮናዊ ንቅናቄ እና አንድ ኢትዮጵያ ዲሞክራሲያዊ ፓርቲ ሐምሌ ፭ ቀን ፳፻፲፭ ዓ.ም ባወጣነው ዚጋራ መግለጫ በአገራቜን እዚተስተዋለ ያለውን ውስብስብ ቜግር ለመፍታትና ዚአገራቜንን ህልውና ለመታደግ አስ቞ኳይ ዹአገር አድን እርምጃ ሊወሰድ እንደሚገባ ለኢትዮጵያ ሕዝብ ግልጜ ያደሚግን ሲሆን ይህንኑ ዚሚገልጜ ደብዳቀ በአድራሻ ማስገባታቜን ይታወሳል። በዚህም መግለጫ እና ደብዳቀ ዚሰላሳ ሁለት ዓመታት እኩይ ዘር ፍሬ ለሆነውና ዛሬ ላይ አገራቜን ለተደቀነባት ሁለንተናዊ ቜግር ብ቞ኛ መፍትሄሔ በምትመሩት መንግሥት፣ ነፍጥ አንስተዉ ዉጊያ ላይ በሚገኙ ኃይሎቜ እና ሕጋዊ እውቅና ኖሯ቞ው በሚንቀሳቀሱ ዚፖለቲካ ፓርቲዎቜ መካኚል አስ቞ኳይ ዹአገር አድን ውይይት ማድሚግ መሆኑን በመግለጜ ይኾው አገር አድን ውይይት አንድ ወር ባልበለጠ ጊዜ እንዲጀመር መጠዚቃቜን ይታወሳል። ይሁን እንጂ ጥያቄያቜንን ካቀሚብን ኚሶስት ሳምንታት በላይ ዹተቆጠሹ ቢሆንም አገርን ኹኹፋው አደጋ ለመታደግ ያለመውን ማሳሰቢያቜንን ጆሮ ዳባ ልበስ በማለት ይልቁን እልህና ፉክክር ዹተላበሰ በሚመስል መልኩ ግጭቱ እዚሰፋ መጥቶ መላው ዚአማራ ክልል ወደ ጩር አውድማነት እዚተለወጠ መሆኑን እዚተመለኚትን ነው። በዚህ ጊርነት መሣሪያ ያልታጠቁ ንጹሐን ዜጎቜም ሕይወት እያለፈ መሆኑንፀ ብሔራዊ ፈተና ዹሚፈተኑ ተማሪዎቜም ላይ በዚሁ ምክንያት መተጓጎል እንደደሚሰባ቞ው ለመሚዳት ቜለናል።

አገር ትምህርት መውሰድ ያለባት ኹሌላ ሳይሆን ዚአንድ ሚሊዹን ልጆቿን ህይወት ኹቀጠፈው ዹሰሜን ኢትዮጵያ ጊርነት ሊሆን እንደሚገባ በማመን አገራቜን ላይ ላንዣበበው ዹኹፋ አደጋ ብ቞ኛ መፍትሄ አስ቞ኳይ ሁሉን አቀፍ ውይይት መሆኑን ዛሬም አጜንኊት ሰጥተን በደጋሚ ልናሳስብና ዛሬ ነገ ሳይባል መንግሥት ራሱን ዝግጁ አድርጎ በገለልተኛ አገር ውይይት እንዲጀመር አጥብቀን እንጠይቃለን። መንግሥት ድጋሚ ያቀሚብነውንና ለአገር ባጠቃላይ እንዲሁም በሥልጣን ላይ ላለው መንግሥት መውጫ መንገድ ሆኖ ሊያገለገል ዚሚቜለውን ይህን ዹአገር አድን ውይይት ሃሳብ ቾል በማለት በሚወስደው ዹኃይል እርምጃ እና ይህን ተኚትሎ ለሚደርሰው ጉዳት ሙሉ ተጠያቂነት እንደሚወስድ አጜንኊት ሰጥተን እናሳስባለን።

እግዚአብሔር ኢትዮጵያንና ሕዝቧን ይጠብቅ!

መኢአድ፣ ኢህአፓ፣ እናት ፓርቲ፣ ዚዐማራ ግዮናዊ ንቅናቄ እና አንድ ኢትዮጵያ ዲሞክራሲያዊ ፓርቲ

04/08/2023

ዹሾኔ ታጣቂዎቜ በጉራጌ ዞን ቡኢ ኹተማ በሚገኝ ፖሊስ ጣቢያ ላይ ጥቃት መፈጾማቾው ተገለጾ

በደቡብ ክልል በጉራጌ ዞን ዚሶዶ ወሚዳ ዋና መቀመጫ በሆነቜው ቡኢ ኹተማ ራሱን ዚኊሮሞ ነጻነት ሠራዊት ብሎ ዚሚጠራው እና በመንግሥት “ኩነግ ሾኔ” በሚል በአሞባሪነት ዹተፈሹጀው ኃይልፀ በኹተማው በሚገኘው ፖሊስ ጣቢያ ላይ ጥቃት መፈጾሙን ነዋሪዎቜ ለአዲስ ማለዳ ገልጞዋል፡፡

ታጣቂዎቹ ጥቃቱን ዚተፈጞሙት በሚቡዕ ሐምሌ 26/2015 ሌሊት አምስት ሰዓት ገደማ መሆኑን ዚጠቆሙት ነዋሪዎቹፀ ጥቃቱ በፖሊስ ጣቢያው ዚታሰሩ ኹ30 በላይ ዚሜብር ቡድኑን አባላት ለማስፈታት መሆኑን ተናግሚዋል፡፡

ዚታጣቂ ቡድኑ አባላት ወደ ኹተማው ዚገቡት በሞተር ሳይክልና በባጃጅ ተሞኚርካሪዎቜ መሆኑን ጠቅሰውምፀ ኚፖሊስ ጣቢያው ጠባቂ ፖሊሶቜ ጋር ለአንድ ሰዓት ያህል ዹዘለቀ ዚተኩስ ልውውጥ ማድሚጋ቞ውን ገልጞዋል፡፡

04/08/2023

አርቲስት አብርሃም ወልዮ እና ባለቀቱ ወ/ሮ ማክዳ ኃ/ሚካኀል 1.9 ሚሊዮን ብር ድጋፍ አደሹጉ!!

አርቲስት አብርሃም ወልዮ እና ባለቀቱ ወ/ሮ ማክዳ ኃ/ሚካኀል በጋብቻ቞ው ወቅት በጎፈንድሚ እና በሀገር ውስጥ ባንኮቜ ያሰባሰቡትን ገንዘብ ለ4 አካባቢዎቜ ድጋፍ አደሚጉ።

👉 ሰቆጣ ለሚገኙ ተፈናቃዮቜ አንድ ሚሊዮን ብር
👉 ደብሚ ብርሃን ለሚገኙ ተፈናቃዮቜ 400,000 ብር
👉 በጉራጌ ዞን እዣ ወሚዳ ለሚገኘው ጋበር በጎ አድራጎት ድርጅት 250,000 ብር
👉 ፊቌ ሰላሌ ለሚገኘው ፍቅር ዹተቀናጀ ዚማህበሚሰብ ዚልማት ድርጅት 250,000 ብር ድጋፍ አድርጓል።

ኹዚህ ቀደም ለመቄዶኒያ ዹ300ሺ ብር ድጋፍ ማድሚጋ቞ው ይታወሳል።

ድጋፉ እስካሁን ዹቆዹው በጎፈንድሚ ዹተሰበሰበው ገንዘብ ለአሞባሪ ነው በማለት ሰዎቜ ሪፖርት ስላደሚጉ ገንዘቡን ለማስለቀቅ ሹጅም ጊዜ እንደወሰደ አርቲስት አብርሃም ወልዮ ተናግሯል።

Want your business to be the top-listed Media Company in Addis Ababa?
Click here to claim your Sponsored Listing.

Address


Addis Ababa
Addis Ababa