Fune Media

Fune Media

Share

Ethiopia

Photos from Fune Media's post 17/06/2026

በሰሜን ወሎ ዞን በጫካ የነበሩ ታጣቂዎች የሰላም አማራጭን እየተቀበሉ ነው።

በሰሜን ወሎ ዞን በጫካ የሚንቀሳቀሱ ታጣቂዎች በየጊዜው መንግሥት ያቀረበውን የሰላም አማራጭ እየተቀበሉ መኾናቸውን የዞኑ ሰላም እና ጸጥታ መምሪያ አስታውቋል።

የሰሜን ወሎ ዞን ሰላም እና ጸጥታ መምሪያ ምክትል ኀላፊ ፈለቀ ጌትነት መንግሥት ከማኅበረሰቡ ጋር ባደረጋቸው ውይይቶች ሰላምን ለማረጋገጥ መግባባት ላይ መደረሱን አስታውሰዋል። በዚህ መሠረትም ማኅበረሰቡ የሰላምን አስፈላጊነት እና የግጭትን አስከፊነት ለታጣቂዎች በማስረዳት ወደ ሰላም እንዲመለሱ እገዛ እያደረገ እንደሚገኝ ተናግረዋል።

መንግሥት የሰላም ጥሪ ካቀረበ በኋላ በተሳሳተ መንገድ ጫካ ገብተው የነበሩ በሺህዎች የሚቆጠሩ ታጣቂዎች የሰላም አማራጭን እንደተቀበሉ ተናግረዋል። ከእነዚህ ውስጥ ከ80 በመቶ በላይ የሚኾኑት የተሃድሶ ሥልጠና እንዲያገኙ ተደርጓል ብለዋል።

ሥልጠናውን ወስደውም የመንግሥት ሥራ የነበራቸው ወደ ቀድሞ ሥራቸው እንዲመለሱ፣ ያልነበራቸው የሥራ ዕድል ተጠቃሚ እንዲኾኑ እየተደረገ ነው ብለዋል።

ትግሉ የውጭ ባዕዳን እና የውስጥ ባንዳ እየተጠቀሙበት ያለ ትግል መኾኑን እየተረዱ በርካቶች አሁንም የሰላም አማራጩን እየተቀበሉ እንደሚገኙም ነው የጠቀሱት። ወደ ሰላም የሚመለሱ ታጣቂዎችንም ሥልጠና እንዲያገኙ በማድረግ የልማት እና የሰላም አርበኛ የማድረግ ሥራው ተጠናክሮ ቀጥሏል ብለዋል።

የሰላም አማራጩን የተቀበሉ የቀድሞ ታጣቂዎች ጫካ የሚገኙ ወጣቶችን በማሳመን ሰላም እንዲሰፍን ተጨማሪ አቅም ኾነው እየሠሩ እንደሚገኙም አመላክተዋል።

የሀገር ሽማግሌዎች እና የሃይማኖት አባቶች ጫካ የወጡት ታጣቂዎች የሰላም ጥሪውን እንዲቀበሉ ከማድረግ በተጨማሪ ከማኅበረሰቡ ጋር እርቀ ሰላም እንዲፈጽሙ እና የተጣሉ እንዲታረቁ በማድረግ ሰላማዊ ሕይወታቸውን እንዲቀጥሉ በማድረግ ለዞኑ ሰላም መስፈን ጉልህ ሚና እየተጫወቱ መኾናቸውን ተናግረዋል። ይህንንም አጠናክረው መቀጠል አለባቸው ነው ያሉት።

በተሳሳተ አመለካከት ጫካ የወጡትን ወጣቶች ወደ ሰላም ለመመለስ የተሠራው ሥራ ውጤት እየተገኘበት ነው ያሉት ምክትል ኀላፊው አሁን ላይ ሰሜን ወሎ ዞን አንፃራዊ ሰላም እየታየበት መኾኑንም ተናግረዋል።

አሚኮ

17/06/2026
17/06/2026

የደቡብ አፍሪካ ትላልቅ የሰራተኛ ማህበራት ሰራተኞች ከፀረ-ስደተኞች ተቃውሞ እንዲርቁ እያሳሰቡ ሲሆን ስራቸውን ቢያቆሙ መዘዝ ሊያጋጥማቸው እንደሚችል አስጠንቅቀዋል። ይህ ጥሪ የመጣው ፀረ-ስደተኞች ቡድኖች የሰኔ 30 ቀን ሰነዳቸውን ለቀው እንዲወጡ ባወጡት የጊዜ ገደብ ምክንያት ውጥረት እየጨመረ በመምጣቱ ነው። ወደ 2 ሚሊዮን የሚጠጉ ሰዎችን የሚወክለው የደቡብ አፍሪካ የሰራተኛ ማህበራት ኮንግረስ (COSATU) ጨምሮ አራት ዋና ዋና ማህበራት ስደተኞች ለአገሪቱ ተግዳሮቶች ተጠያቂ መሆን እንደሌለባቸው ተናግረዋል፣ እነሱን ማስወገድ ስራ አጥነትን፣ የህዝብ አገልግሎቶችን ወይም የኢኮኖሚ ችግሮችን እንደማያስተካክል አፅንዖት ሰጥተዋል። ማህበራት ፕሬዝዳንት ሲሪል ራማፎሳ ማክሰኞ ዕለት በደቡብ አፍሪካ ችግሮች ስደተኞችን ላለማስጨነቅ የሰጡትን ጥሪ አስተጋብተዋል።

Photos from Fune Media's post 17/06/2026

የአሜሪካው ፕሬዝዳንት ዶናልድ ትራምፕ በፈረንሳይ በሚካሄደው የቡድን 7 ጉባኤ ላይ ከግብፅ ፕሬዝዳንት አብደል ፋታህ ኤልሲሲ ጋር የንግድ ጉዳዮችን እና በታላቁ የኢትዮጵያ ህዳሴ ግድብ ላይ ስላለው አለመግባባት እንደሚወያዩ ተናግረዋል።

Photos from Fune Media's post 16/06/2026

ከሁሉ አስቀድሜ ከሕልም ሌሊት ጅማሮ እስከ ስኬት ንጋት ድረስ የሕይወታችን ደራሲ፣ የበረከታችን ምንጭ እና የድል ሁሉ ባለቤት የሆነው ሁሉን ቻይ እግዚአብሔር የተመሰገነ ይሁን።

ዛሬ እዚህ የተሰበሰብነው አንድ ሕንፃ ለመጀመር ብቻ አይደለም። ተስፋን ለመትከል፣ ዕድልን ለመፍጠር እና ለትውልድ የሚተላለፍ ቅርስ ለመገንባት ነው።
የማስተር አብነት ከበደ ፋውንዴሽን የተቋቋመው ከሕይወት ጉዞአችን የተማርናቸውን ትምህርቶች በተግባር ለመተርጎም ነው። በብዙ ስፍራዎች ተስፋ የሚፈልጉ ወጣቶችን፣ ድጋፍ የሚሹ ሕፃናትን፣ እገዛ የሚያስፈልጋቸውን ቤተሰቦችን እና ዕድል የሚጠባበቁ ማኅበረሰቦችን በማየታችን ይህን ራዕይ ተሸክመን ተነስተናል።

ራዕያችን በእውቀት የበለጸገ፣ በእሴት የተመራ፣ በፍትህ የተገነባ እና ለሁሉም እኩል ዕድል የሚሰጥ ማኅበረሰብ ማየት ነው።

ዛሬ የምናኖረው የመሠረት ድንጋይ የሲሚንቶና የድንጋይ ክምር ብቻ አይደለም። ይህ የተስፋ መሠረት ነው፤ የአገልግሎት መሠረት ነው፤ የለውጥ መሠረት ነው።
ስለዚህ ይህ ፋውንዴሽን የአንድ ሰው ወይም የአንድ ቡድን ንብረት ሳይሆን የሁላችንም የጋራ እንደመሆኑ በአንድነት ስንቆም ራዕዩ በህያዉነት ይቀጥላል።

በዚህ አጋጣሚ ለከምባታ ዞን አስተዳደር፣ ለቀዲዳ ጋሜላ ወረዳ አስተዳደር፣ ለሃይማኖት አባቶች፣ ለአገር ሽማግሌዎች እና ለዚህ ራዕይ እውን እንዲሆን ድጋፍና ትብብር ላደረጋችሁልን ሁሉ ከልብ የመነጨ ምስጋናዬን እናቀረብኩ ሁላችሁንም የዚህ ታላቅ ራዕይ ተሳታፊዎች፣ ደጋፊዎች እና አጋሮች እንድትሆኑ የክብር ጥሪ አቀርባለሁ።

እግዚአብሔር ይህን ፋውንዴሽን ይባርክ፤
እግዚአብሔር አገራችንን ይባርክ፤
እግዚአብሔር ሕዝባችንን ይባርክ።
አመሰግናለሁ!

15/06/2026

June 14/2026 eNCA ላይ በነበረኝ ቆይታ ካነሳኋቸው ነጥቦች....
* "ከJune 30 በፊት ውጡ" ብንባልም የምንሄድበት ስለሌለን የደቡብ አፍሪካ መንግስት እና ህዝብ ይረዳ*ናል ብለን እናምናለን!
* ጦርነት ሸሽተን ነው የመጣነው:: በኢትዮጵያ እስከ አሁን ግጭት እያለ እንዴት ብለን እንመለሳለን?!
*Spaza Shop ውስጥ ብዙ ኢትዮጵያዊያን በተለይም ከሀድያ እና ከምባታ ማህበረሰብ ተገድለውብንም ነው በአገሪቱ ወንጀል ስላለ እና ዜጎችም የዚህ ሰለባ ስለሆኑ ምንም ሳንል የምንኖረው!
* የSpaza Shop ስራ ትልቅ ገቢ የሚያስገኝ ሳይሆን ኑሮ ለመግፋት የሚሰራ ስራ ነው። ከደቡብ አፍሪካዊያን ምንም ስራ አልወሰድንም!
* ለመኖሪያ ወረቀት ስናመለክት ከመንግሥት/Home Affairs Covid-19 ቀጥሎ Backlog (ብዙ ማመልከቻ መኖር) እንደምክንያት እየተነገረን ቆይቶ አሁን ደግሞ ህገ-ወጥ ናችሁ እየተባልን ነው። ይህ ልክ አይደለም!
* Spaza Shop Registration ምን ላይ እንደደረሰ የተነገረን ነገር የለም! እኛ የተባልነውን ሁሉ አድርገናል!
*ከጦርነት ሽሽት መሰደድ፣ የመኖርያ ፈቃድ መጠየቅ፣ ጉዳያችን እስኪጣራ መጠበቅ ወንጀል ነው ወይ? ምንም ሳናጠፋ ህገወጥ ናችሁ ውጡ መባላችን ልክ አይደለም!

15/06/2026

ዶ/ር ቴድሮስ ደቡብ አፍሪካ ውስጥ በተገደለ ኢትዮጵያዊ ጉዳይ የሰጡት አስተያየት ያስነሳው ቅሬታ

የዓለም ጤና ድርጅት ዋና ዳይሬክተር ዶክተር ቴድሮስ አድሃኖም ደቡብ አፍሪካ ውስጥ በተገደሉ ኢትዮጵያዊ እና ሞዛምቢካዊ ዙሪያ በሰጡት አስተያየት የአገሪቱ መንግሥት ደስተኛ አለመሆኑን ገለጸ።

ዶክተር ቴድሮስ እሁድ ዕለት ደቡብ አፍሪካ ውስጥ "ሌላ ዙር መጤ ጠል ጥቃት" እያገረሸ መሆኑን በመጥቀስ ድርጊቱ "አገሪቱ ለነጻነት ያደረገችውን ትግል የሚክድ አሳዛኝ" ሁኔታ ነው በማለት ገልጸው ነበር።

የዓለም ጤና ድርጅት ዋና ዳይሬክተር በደቡብ አፍሪካ ውስጥ በሚፈጸሙ መጤ ጠል ጥቃቶች የሰው ሕይወት በአጭሩ እየተቀጨ መሆኑን በመግለጽ፣ በቅርቡ የሞቱ ኢትዮጵያዊ እና ሞዛምቢካዊ ዜጎችን በምሳሌነት ጠቅሰዋል።

ይህንንም ተከትሎ የደቡብ አፍሪካ ባለሥልጣናት የዋና ዳይሬክተሩ አስተያየት ትክክል አለመሆኑን በመጥቀስ በአገሪቱ ውስጥ ተፈጥሯል ስለሚባለው መጤ ጠል ጥቃት ትክክለኛ እና አስተማማኝ መረጃን ለዓለም ጤና ድርጅት ለማስረዳት እንደሚፈልጉ ገልጸዋል።

ዓለም አቀፍ ግንኙነት እና ትብብር መሥሪያ ቤት የሚባለው የደቡብ አፍሪካ የውጭ ጉዳይ ሚኒስቴር ቃል አቀባይ ለቢቢሲ እንደተናገሩት፤ ዶክተር ቴድሮስ የጠቀሷቸው የውጭ ዜጎች ሕይወት በማለፉ እንደሚያዝኑ በመግለጽ ምክንያቱ ግን መጤ ጠል ጥቃት እንዳልሆነ አስተባብለዋል።

ባለሥልጣናት ለኢትዮጵያዊው እና ለሞዛምቢካዊው ሞት ምክንያቱ የመጤ ጠል ጥቃት አለመሆኑን ከመገልጻቸው በተጨማሪ፤ የኢትዮጵያዊው ሞት ከተደራጀ ወንጀል ጋር እንደሚያያዝ፣ የሞዛምቢካዊው ሞት ደግሞ ምርመራ እየተደረገበት እንደሆነ አሳውቀዋል።...(BBC Amharic)

15/06/2026

እድለኛ ነፍስ!

ሚሊዮን አብይ አህመድ እና አብይ አህመድ አሊ!

Photos from Fune Media's post 10/06/2026

አሜሪካ እንዳይገባ የታገደው ሶማሊያዊ ዳኛ ወደ ሀገሩ ሲመለስ አቀባበል ተደረገለት

የዓለም ዋንጫ ጨዋታዎችን በዳኝነት እንዲመራ ተመርጦ አሜሪካ እንዳይገባ የታገደው ሶማሊያዊ ዳኛ ኦማር አርታን ወደ ሀገሩ ሲመለስ ደማቅ አቀባበል ተደርጎለታል፡፡

የ2026 ዓለም ዋንጫ ጨዋታዎችን በዳኝነት እንዲመራ የተመረጠው ሶማሊያዊ ዳኛ ኦማር አርታን ወደ አሜሪካ አቅንቶ ነበር፡፡

ይሁን እንጂ በዓለም ዋንጫ የመጀመሪያው ሶማሊያዊ ዳኛ ይሆናል ተብሎ ሲጠበቅ የነበረው ኦማር አርታን አሜሪካ ሲደርስ ያልጠበቀው ነገር ተከሰተ፡፡

በፈረንጆቹ 2025 የአፍሪካ የዓመቱ ምርጥ ዳኛ የተባለው ኦማር ማያሚ አውሮፕላን ማረፊያ ከደረሰ በኋላ ወደ አሜሪካ መግባት እንደማይችል ተነግሮታል፡፡

እድል ያልቀናው ኦማር አርታን ወደ እናት ሀገሩ ሶማሊያ ሲመለስም የሀገሪቱ ፕሬዚዳንት ሀሰን ሼክ መሃሙድ በቤተ መንግሥታቸው ደማቅ አቀባበል አድርገውለታል፡፡

በተጨማሪም ለዳኛ ኦማር አርታን ሌሎች የሀገሪቱ ከፍተኛ አመራሮች እና የሞቃዲሾ ከተማ ነዋሪዎች ደማቅ አቀባበል በማድረግ አጋርነታቸውን አሳይተዋል፡፡

ፕሬዚዳንት ሀሰን ሼክ መሃሙድ ዳኛ ኦማር እስካሁን ላሳየው ስኬት እንዲሁም ለሀገሩ ላበረከተው አስተዋጽኦ አመስግነዋል፡፡

በቀጣይ ለሚያከናውነው ሥራ ከጎኑ መሆናቸውንም አረጋግጠዋል፡፡

ፊፋ የአሜሪካ ባለስልጣናትን በጉዳዩ ላይ ካነጋገረ በኋላ ዳኛው በውድድሩ ላይ በዳኝነት እንደማይሳተፍ ይፋ ማድረጉን ቢቢሲ ዘግቧል፡፡

09/06/2026

የሱዳን የሴቶች ቡድን በኦሎምፒክ ማጣሪያ ከኮሞሮስ ጋር 30-0 ሽንፈት ደርሶበታል🤔

ወይኔ በላቸው 🤔😃

የሱዳን ብሔራዊ የሴቶች እግር ኳስ ቡድን በ2028 የሎስ አንጀለስ የሴቶች የኦሎምፒክ እግር ኳስ ውድድር የአፍሪካ ማጣሪያ ጨዋታ ላይ ከኮሞሮስ ጋር አሳፋሪ 30-0 ሽንፈት ደርሶበታል።

Want your business to be the top-listed Photography Service in Addis Ababa?
Click here to claim your Sponsored Listing.

Category

Website

Address


Addis Ababa