Doch HD
DOCH [Digital Outlet for Creative Hits]
Positive Vibes Only
________________________
❚█Your Hate Comments Are REMOVED█❚
Doch HD ገና በጅምር ላይ ያለ የመረጃና የመዝናኛ ሚዲያ ነው። በዚህም መረጃ ሰጪ ቪዲዮ እና ምስል እንዲሁም ፅሁፍ በየቀኑ በየሰዓቱ ከእኛ ይመልከቱ። ዶች
12/05/2026
በክልሉ ካፋ ዞን ቦንጋ ከተማ የብልጽግና ፓርቲ የድጋፍ ሰልፍና የምረጡኝ ቅስቀሳ በነገው እለት ይካሄዳል 🔥
በደቡብ ምዕራብ ኢትዮጵያ ህዝቦች ክልል ካፋ ዞን የቦንጋ ከተማ አስተዳደር ብልፅግና ፓርቲ ቅ/ጽ/ቤት ኃላፊ አቶ ፍሬው አበበ በነገው ዕለት በወጣቶች ማህበራዊ መሠረት የሚደረገውን የብልጽግና ፓርቲ ድጋፍ ሰልፍ እና ቡና ጠጡ ፕሮግራም አስመልክቶ መልዕክት አስተላልፈዋል።
በነገው ዕለት በወጣቱ የሚካሄደው የድጋፍ ሰልፍ ባለፉት ዓመታት የተመዘገቡ ስኬቶችን ለማስቀጠልና የሚታዩ ማህበራዊ ተግዳሮቶችን በጋራ ለመፍታት ያለንን ቁርጠኝነት የሚያሳይ የድጋፍ ሰልፍ መሆኑን አቶ ፍሬው አብራርተዋል።
ሰልፉ ከፖለቲካዊ ድጋፍ ባለፈ በወጣቶች መካከል ያለውን ማህበራዊ ትስስር ወንድማማችነትና እህትማማችነት ለማጎልበት ያለመ መሆኑን ነው አቶ ፍሬው የተናገሩት።
ወጣቱ በሁሉም ማህበራዊ ጉዳዮች የሚጠበቅበትን በመወጣት ንቁ ተሳትፎ እንዲያደርግ ጥሪያቸውን አስተላልፈዋል።
የከተማ አስተዳደሩ የወጣቶችን ማህበራዊ ጥያቄዎች ደረጃ በደረጃ ለመመለስ ሌት ተቀን እየሰራ ይገኛል ያሉት አቶ ፍሬው ይህ የድጋፍ ሰልፍ ለኛ ተጨማሪ ጉልበት የሚሰጠን ሲሆን፣ በቀጣይም በከተማችን ለሚከናወኑ ፕሮጀክቶችና የልማት ስራዎች ወጣቱ የባለቤትነት ሚናውን እንዲወጣ ጥሪ አቀርባለሁ ብለዋል።
ዶች ኤችዲ
12/05/2026
የፈረንሣይ ኤምባሲ ብሩክን አደነቀ 🔥
በማህበራዊ ሚዲያ በሚያቀርባቸው ፈጣንና ተአማኒነት ያላቸው መረጃዎች በማቅረብ የሚታወቀው ብሩክ ጫላ (ብሩክ ኒውስ) በፈረንሳይ ኤምባሲ አድናቆት ቀርቦለታል።
ኤምባሲው ባወጣው መረጃው ብሩክ በኢትዮጵያ በሚሊዮን የሚቆጠር ምልከታ ያላቸውን ይዘቶች የሚፈጥር መሆኑን በመጥቀስ በአጫጭር መረጃዎችና በሚያቀርባቸው ሃሳቦች ይታወቃል ብሏል።
ይህ የይዘት ፈጣሪ በኬኒያ ናይሮቢ በመካሄድ ላይ የሚገኘውን በኢኖቬሽን፣ በወጣቶች እንዲሁም የአፍሪካና ፈረንሳይ አጋርነት ላይ ያተኮሩ መረጃዎችን በቅርበት ለብዙሃን አድርሷል ብሏል።
ዶች ኤችዲ
12/05/2026
በክልሉ ካፋ ዞን ጊምቦ ወረዳ የ1.5 ሚሊዮን ብር ፕሮጀክት ሲመረቅ ለሌላው የመሠረት ድንጋይ ተቀመጠ 🔥
በደቡብ ምዕራብ ኢትዮጵያ ህዝቦች ክልል ካፋ ዞን ጊምቦ ወረዳ ከ1.5 ሚሊዮን ብር በላይ በሆነ ወጪ በማህበረሰቡ ንቁ ተሳትፎ የተገነባው የድሪ ክላስተር ማህበረሰብ አቀፍ ፖሊስ አገልግሎት መስጫ ማዕከል በዛሬው እለት ተመርቆ ለአገልግሎት ክፍት ሆኗል።
በምረቃው ስነ-ስርዓት ላይ የተገኙት የካፋ ዞን ዋና አስተዳዳሪ አቶ እንዳሻው ከበደ ጊምቦ ወረዳ በተለያዩ የልማት ዘርፎች ሞዴል መሆኑን ጠቅሰው፣ የፖሊስ ማዕከሉ መገንባት ለአካባቢው ሰላምና ለሚከናወኑ የዕድገት ጉዞዎች መፋጠን ትልቅ ፋይዳ እንዳለው ገልጸዋል።
የወረዳው አስተዳዳሪ አቶ ትብብሩ አሰፋ በበኩላቸው ማዕከሉ በአቅራቢያ መገንባቱ ወንጀልን ለመቆጣጠርና ማህበረሰቡን ከእንግልት ለመታደግ እንደሚረዳ አስረድተዋል።
በተመሳሳይ ዕለት የድሪ መለስ ዜናዊ ሁለተኛ ደረጃ ትምህርት ቤት የመማሪያ ክፍል ማስፋፊያ ግንባታ የመሰረተ ድንጋይ በደመቀ ሁኔታ ተቀምጧል።
አቶ ትብብሩ በዚህ ወቅት ባደረጉት ንግግር የመሰረተ ድንጋይ የተቀመጠለት የትምህርት ቤት ማስፋፊያ ግንባታም ተፅዕኖ ፈጣሪ ትውልድ ለማፍራት የሚደረገውን ጥረት የሚያግዝ መሆኑን አስታውቀዋል።
በትምህርት ቤቱ ግንባታ መጀመር የተደሰቱት የአካባቢው ነዋሪዎችና ጥሪ የተደረገላቸው የመንግስት ከፍተኛ አመራሮችም የነገዋን ሀገር ተረካቢ ትውልድ ለመፍጠር የጀመሩትን የልማት አሻራ አጠናክረው እንደሚቀጥሉ ተናግረዋል።
ዶች ኤችዲ
12/05/2026
በክልሉ ካፋ ዞን ህገወጥ ተሽከርካሪዎችና አሽከርካሪዎች ላይ እርምጃ መውሰድ ተጀመረ🔥
በደቡብ ምዕራብ ኢትዮጵያ ህዝቦች ክልል የካፋ ዞን መንገድና ትራንስፖርት መምሪያ ከቀናት በፊት ባወጣው ማስታወቂያ በዞኑ በሚገኙ የተሽከርካሪ ማህበራት ሥር ባሉ ህዝባዊ አገልግሎት መስጠት ያቆሙ አሽከርካሪዎች ላይ እርምጃ እንደሚወስድ አስጠንቅቆ እንደነበር ይታወሳል።
በዚህ መሠረት በዞኑ ደካ ከተማ አስተዳደር ፖሊሲ ጽ/ቤት በደካ መናኸሪያ 'ናፍጣ የለም' በሚል ሰበብ የህዝብ አገልግሎት መስጠት ማቆም በቀጠሉ የህዝብ ማመላለሻ ተሽከርካሪዎች ላይ እርምጃ ወስዷል።
በዚህም 16 የህዝብ ማመላለሻ ተሽከርካሪዎች መርሃግብር ባለመሽፈን እያንዳንዳቸው 6000 ሺህ ብር የተቀጡ ሲሆን አንድ ተሽከርካር ከስምሪት ታግዷል።
በተጨማሪ ከስምሪት የታገደው ተሽከርካሪ ባለንብረትም በህግ ቁጥጥር ስር በማዋል ምርመራ እየተደረገበት እንደሚገኝ የደካ ከተማ አስተዳደር የመንግስት ኮሙኒኬሽን ዘግቧል ።
ዶች ኤችዲ
12/05/2026
የካፋው ቴንጌ ቴንጌ ከወንድሜ አገናኙኝ ብሏል 🔥
ይህ በምስሉ ላይ የሚታየው ታዳጊ በደቡብ ምዕራብ ኢትዮጵያ ህዝቦች ክልል ካፋ ዞን የጠሎ ወረዳ ተወላጅ ነው። ታዳጊው በጫማ ማሳመር ሥራ (ሊስትሮ) የሚተዳደር ሲሆን ከኡጋንዳዊው ታዋቂ የይዘት ፈጣሪ ራንጎ ቴንጌ ቴንጌ (Rango Tenge Tenge ) ባለው የፊት ገፅታ መመሳሰል 'ወንድሜን አገናኙኝ' ብሏል።
ዶች ኤችዲ
12/05/2026
በክልሉ ገቢን በአግባቡ በመሰብሰብ የልማት ፍላጎትን ማሳካት እንደሚገባ ርዕሰ መስተዳድር ነጋሽ ተናገሩ 🔥
የደቡብ ምዕራብ ኢትዮጵያ ህዝቦች ክልል የ2018 የእስካሁን ገቢ አፈፃፀምና ቀጣይ አቅጣጫዎች ላይ ያተኮረ የባለድርሻ አካላት የውይይት መድረክ ርዕሰ መስተዳድር ኢንጂነር ነጋሽ ዋጌሾ (ዶ/ር) በተገኙበት በቦንጋ ከተማ ተካሂዷል።
በክልሉ የልማት ፍላጎት በከፍተኛ ሁኔታ እያደገ በመሆኑ ይህን የመልማት ፍላጎት በአግባቡ መመለስ የሚቻለው ኢኮኖሚ በሚያመነጨው ሀብት ልክ ገቢን መሰብሰብ ሲቻል ብቻ በመሆኑ የገቢ አሰባሰብ ስራ በቅንጅትና በኃላፊነት መንፈስ ልፈፀም ይገባል ብለዋል።
ገቢ አሰባሰብ ወቅት የሚታዪ ማጭበርበሮችን ለመከላከል በተለይ ዘርፉን በቴክኖሎጂ ማስደገፍና የኦዲት ስርዓትን ማጠናከር እንደሚገባም ጠይቀዋል። የባለሙያዎችን የስነምግባር ችግር ለመቅረፍ ጥብቅ እርምጃዎችን መውሰድ እንደሚገባና አቅማቸውን ለማሳደግ ተከታታይ ግንዛቤዎችን መስጠት እንደሚገባም ገልፀዋል።
በበጀት ዓመቱ ከማዘጋጃ ቤታዊ አገልግሎት፥ታክስ ያልሆኑ ገቢዎችና የገጠር መሬት መጠቀሚያ ግብር አፈፃፀም ዝቅተኛ በመሆኑ የበጀት ዓመቱን እቅድ ለማሳካት በልዩ ቁርጠኝነት ልሰራ ይገባል ብለዋል።
በኦዲት የተገኘውን ታክስና ውዝፍ እዳዎችን በተቀመጠው አጭር ጊዜ በማስፈፀም የገቢ ጉድለቶችን መሙላትም ትኩረት ልደረግበት እንደሚገባ ርዕሰ መስተዳድሩ በአፅንኦት ጠይቀዋል።
የክልሉ ገቢዎች ቢሮ ኃላፊ ወ/ሮ ህይወት አሰግድ በበኩላቸው ቢሮው የግብር ህግ ተገጂነትን ለማስከበርና የሰራተኞችን አቅም በማሳደግ የክልሉን ገቢ አቅም ለማሳደግ አልሞ እየሰራ ይገኛል ብለዋል። የባለሙያዎች የአቅም ክፍተትና የአሰራር ብልሹነትን ለማወቅ ልዩ የግምገማ ስርዓት ተዘጋጅቶ የስነምግባር ጉድለት የገጠማቸው ባለሙያዎችን አስተዳደራዊና ህጋዊ እርምጃዎችን የሚወስድ ስራ ተጠናክሮ እየተሰራ ይገኛል ብለዋል።
የገቢ አሰባሰብ ስርዓትን በቴክኖሎጂ ለማስደገፍ የካሽ ሪጅስተር ማሽኖችን የማቅረብ ስራ በትኩረት እየተሰራ መሆኑን የጠቆሙት ኃላፊዋ ማሽኑ በተለይ ከተጨማሪ እሴት ታክስ የሚገኘውን የገቢ አቅም ከማሳደግ አንፃር ትልቅ ድርሻ ይኖረዋል ብለዋል። ተጨማሪ እሴት ታክስ አፈፃፀም ላይ የሚታየውን ክፍተት ለመሙላት በተለይ ተገልጋዮች ከሆቴሎች፣ ከአገልግሎት ሰጪ ተቋማት ደረሰኝ ጠይቆ የመቀበል ልምድ ማደግ እንዳለበት ጠይቀዋል።
ዶች ኤችዲ
12/05/2026
አላህ ድብድብ አይወድም፤ እናቴም ተው ብላኛለች እናም አልደባደብም ሲል ሴዶ ተናገረ 🔥
በኢትዮጵያ ለሁለተኛ ጊዜ ይካሄዳል ተብሎ የነበረው ድብልቅ ማርሻል አርት ተሰርዟል። ይህም የሆነው ከ5 ሚሊዮን ጥያቄ እስከ 10 ሚሊዮን ብር እንዲሁም የትኬት ሽያጭና የ5 ሚሊዮን ቀብድ ጥያቄዎች በተደጋጋሚ ሀሳቡን በቀየረው ሴዶ ማርሻል ነው።
ሴዶ ትናንት ምሽት በቲክቶክ ላይቭ ባስተላለፈው መልእክት 'አላህ ድብድብ አይወድም' ሲል ፍልሚያውን ላለመፈለጉ ሃይማኖታዊ ምክንያት ሰጥቷል።
በተጨማሪም 'እናቴ ሰምታለች ተውም ብላኛለች' ያለው ሴዶ ለእናቱ ክብር መስጠት በማሰብም በዚሁ ድብድብ እንደማይሳተፍ በይፋ ተናግሯል።
ሴዶ ይህንን ያለው የሚደግፋቸውን የእስልምና እምነት ተከታይ ብዙ የፍልሚያው ስፖርት ሰዎች እያሞካሸ በተናገረበትና 'ወላሂ አደባደባለሁ' ባለበት በዚያው አንደበት መሆኑ 'ፈሪ' እንዲባል አድርጓል።
ዶች ኤችዲ
የንቃተ ህሊና በራስ መተማመን እንዲኖረኝ ነው የምፈልገው🔥
11/05/2026
ጆኒ ለማንያዘዋል የ1 ሚሊዮን ብር ክርክር ጥሪ አቀረበ 🔥
የኢትዮጵያ የመጀመሪያው ድብልቅ ማርሻል አርት አሸናፊው ዮሐንስ ስለሺ (ጆኒ) ከአንድ ፖድካስት ጋር ባደረገው ቆይታ በተከታታይ ሲነቅፈው ለነበረው ማንያዘዋል እሸቱ ጥሪ አቅርቧል።
ማንያዘዋል የቢዝነስ ሰው እንዲሁም አነቃቂ እና የስብዕና ማጎልበቻ አሰልጣኝም በመሆን የሚታወቅ ሲሆን በጆኒ አጠራር " የዓመቱ አሽቋላጭ" ተብሎ መጠራቱ ክብረነክ ተብሎ ሲነሳ ቆይቷል።
ጆኒ በዚሁ ሃሳቡ በመፅናት በፖድካስት ቀርቦ በተናገረው ንግግር 'ማንያዘዋል በመረጠው ርዕስ ቦታና ጊዜ ተሰይሞ ተከራክረን ካሸነፈ 1 ሚሊዮን ብር እሰጠዋለሁ" ሲል ስለሚናገራቸው ነገሮች ጥልቅ እውቀት እንደሌለው ለማሳየት ጥረት አድርጓል።
በማንያዘዋል በኩል የተሰጠ ምላሽ ባይኖርም የኬጅ ፍልማያ ያሸነፈው ጆኒ የሃሳብና እውቀት ክርክሩ ይቀናው ይሆን የሚለው በጊዜ ሂደት የሚታይ ሆኗል።
ዶች ኤችዲ
11/05/2026
የክልሉ የጤናው ዘርፍ ጠንካራ ሥራና እምርታው 🔥
የደቡብ ምዕራብ ኢትዮጵያ ሕዝቦች ክልል ከተመሠረተ ጥቂት ዓመታት ቢቆጠሩም በጤናው ዘርፍ ያስመዘገባቸው እምርታዎች በተጨባጭ የህዝብን የጤና አገልግሎት ጥያቄ በመመለስ ላይ የሚገኙ ናቸው።
የክልሉ ጤና ቢሮ ኃላፊ አቶ ኢብራሂም ተማም፤ የጤና መሠረተ ልማት ተደራሽነትን በማሳደግ ረገድ ባከናወነው ሰፊ ተግባር በአሁኑ ወቅት 12 የመጀመሪያ ደረጃ ሆስፒታሎች እና 5 ጠቅላላ ሆስፒታሎች በድምሩ 17 የመንግስት ሆስፒታሎች አገልግሎት እየሰጡ እንደሚገኙ ተናግረዋል።
ከእነዚህም በተጨማሪ 135 ጤና ጣቢያዎች እና 755 ጤና ኬላዎች በየቀበሌው ተደራሽ በመሆን መሠረታዊ የጤና አገልግሎትን ለኅብረተሰቡ እያቀረቡ እንደሚገኙ ጠቁመዋል።
የጤና ዘርፍ ስኬት ለአንድ አካባቢ ኢኮኖሚያዊ ጥንካሬ እና የዜጎችን ሰብአዊ ሁለንተናዊ ልዕልና የሚያረጋግጥ ትልቅ ምሰሶ መኾኑን የጠቀሱት አቶ ኢብራሂም፤ የግሉ የጤና ዘርፍ ተሳትፎም ለክልሉ የጤና ዘርፍ ስኬት ትልቅ አቅም መሆኑን በማንሳት በግሉ ዘርፍ 4 የመጀመሪያ ደረጃ ሆስፒታሎች እና 1,521 ሌሎች የጤና ተቋማት ጥራት ያለው የሕክምና አገልግሎት በመስጠት ላይ መሆናቸውን አብራርተዋል።
የጤና መረጃ አያያዝን ወደ ዘመናዊ ዲጂታል ሥርዓት ለማሸጋገር በተከናወኑ ተግባራት በክልሉ የሚገኙ ሁሉም የመንግሥትና የግል የጤና ተቋማት በDHIS2 የመረጃ ሥርዓት ውስጥ እንዲካተቱ መደረጉንና በተለይም የኤሌክትሮኒክ ማኅበረሰብ ጤና መረጃ ሥርዓት (eCHIS) በ22 ወረዳዎች በሚገኙ 80 ጤና ጣቢያዎች እና 412 ጤና ኬላዎች ላይ ተዘርግቶ ተግባራዊ መደረጉ የመረጃ ጥራትንና ቅልጥፍናን ለማረጋገጥ ትልቅ አስተዋጽኦ እያበረከተ መኾኑን ኃላፊው አስረድተዋል።
በእናቶችና ሕፃናት ጤና ዙሪያም አገር አቀፍ ተሞክሮ ሊሆን የሚችል ውጤት መመዝገቡን የገለጹት አቶ ኢብራሂም፤ የእናቶች ቀዶ ጥገና አገልግሎት የሚሰጡ ተቋማትን ቁጥር በማሳደግ፣ ከ162 በላይ አምቡላንሶችን በማሰራጨት እና የማኅጸን በር ካንሰር ልየታ ማዕከላትን ከ7 ወደ 44 በማሳደግ የሪፈራል ሥርዓቱና የሴቶች ጤና ጥበቃ እንዲጠናከር መደረጉን ጠቁመዋል።
የወባ ወረርሽኝን ለመከላከልና ለመቆጣጠር በተደረገ ርብርብ የወባ ሞት ምጣኔን በ90 በመቶ መቀነስ መቻሉ ሌላው መጠቀስ ያለበት ስኬት መኾኑንና በዚህም ውጤታማ የአካባቢ ጥበቃ ስራዎችን እና የአልጋ አጎበር ስርጭትን ተግባራዊ በማድረግ የጠቅላላ የታካሚ ቁጥር በ50 በመቶ፣ በተኝቶ ታካሚ ደግሞ በ80 በመቶ መቀነሱን ተናግረዋል።
የማኅበረሰብ አቀፍ የጤና መድህን (CBHI) ተጠቃሚዎች ቁጥር 2.1 ሚሊዮን መድረሱና 83 ከመቶ የሚሆኑ የጤና ባለሙያዎች የማኅበራዊ ጤና መድህን ተጠቃሚ መሆናቸው ለዘርፉ ቀጣይነትና ለባለሙያዎች የሥራ ተነሳሽነት መጎልበት ትልቅ ሚና እንዳለው የገለጹት ኃላፊው፤ የኦክስጅን ማምረቻ ማዕከላትና የደም ባንኮች ቁጥር ወደ 3 ማደጉ እንዲሁም የጤና ባለሙያዎች ቁጥር 11 ሺህ መድረሱ ክልሉ የሕዝቡን የጤና ዋስትና ለማረጋገጥ የሄደበትን ርቀት የሚያሳይ መሆኑን ገልጸዋል።
በአጠቃላይ በደቡብ ምዕራብ ኢትዮጵያ ሕዝቦች ክልል የጤና አገልግሎት ተደራሽነት ከቁጥር ባለፈ በጥራትና በዲጂታል ሥርዓት እየተደገፈ እንደሚገኝ ያመለከቱት አቶ ኢብራሂም፤ በዘርፉ የተመዘገቡ ስኬቶችን በማስቀጠልና የታዩ ክፍተቶችን በመሙላት የክልሉን ሕዝብ የጤና ዋስትና ለማረጋገጥ በትኩረት እየተሰራ መሆኑንና አዳዲስ የጤና ተቋማትን በክልሉ በተለያዩ አከባቢዎች በመገንባት እንዲሁም በተገነቡት ውስጥ በኅብረተሰቡና በባለድርሻ አካላት ትብብር ቁሳቁስ የማሟላት ተግባር እየተከናወነ እንደሚገኝ ጨምረው ገልጸዋል።
ይህ ውጤት በቁርጠኝነት በሚሰሩ አመራሮች የተመዘገበ በመሆኑ የተጀመረውን የልማት ጉዞ ለቀጣይ 5 ዓመታት በተሻለ አቅም ለማስቀጠል የሕዝቡ ያልተቋረጠ ድጋፍና ተሳትፎ ወሳኝ መሆኑን ማንሳት ተገቢ ይሆናል።
ዶች ኤችዲ
11/05/2026
የሴዶ ማርሻል የቴክቶክ አካውንት ተዘጋ
በኢትዮጵያ ሊደረግ ለታቀደው 2ተኛ ድብልቅ ማርሻል አርት በተደጋጋሚ ጥሪ በማድረግ ተመልካቹን ያሰለቸው ሴዶ ማርሻል አካውንቱን አጥቷል።
ሴዶ ከደቂቃዎች በፊት ባስተላለፈው መልእክት ከ100 በላይ ቪዲዮ ሪፖርት እንደተደረገበት ጠቅሶ በአሁኑ ሰዓት አካውንቱን ማጣቱን ተናግሯል።
አካውንቱ ይመለስ አይመለስ የሚታወቅ ነገር ባይኖርም አዘጋጆች መደራደር እየተቻለ ይህንን አደረጉብኝ ሲል በቀጥታ ከተደራዳሪው ላይ ወቀሳ ቢሰነዝርም እርምጃው ከተሰላቸ ተመልካች እንጂ ከእነሱ ላይሆን ይችላል ተብሏል።
ሴዶ ወደ ፍልሚያ ላለመመለሱ ትናንት በአሜሪካ የተደረገው ውድድር ምክንያት ሆኗል የሚሉም ሰዎች አልጠፉም። በዚህ ውድድር ሴዶ የሚደግፈው ተፋላሚ እስከ መድማት የደረሰ የአካል ጉዳት አስተናግዶ በታሪኩ ለመጀመሪያ ጊዜ መሸነፉ ተጨማሪ የስነልቦና ጫና አድርሶበታል ተብሏል።
ዶች ኤችዲ
Click here to claim your Sponsored Listing.
Telephone
Website
Address
Addis Ababa
1000