Value Podcast
This page is designed to bring a Value adding Business tips and Advices!
12/04/2024
The National Bank of Ethiopia classified commercial banks in three categories; large, medium, and small banks, based on their asset.
Capital
Large: the state-owned Commercial Bank of Ethiopia that has a total assets and deposits of 9.5 percent and 48.7 percent, respectively of the whole banking sector at end-June 2023, its.Medium: Awash Bank, Bank of Abyssinia, Cooperative Bank of Oromia, Dashen Bank, Hibret Bank (five banks). Accounted for 28.0 percent of the sector’s total assets, 29.4 percent of deposits and their entire capital was 31.0 percent at the end of June 2023.
Small: 24 banks accounted for 22.5 percent asset and 21.9 percent deposit. Their combined total capital share stood at 41.6 percent at end-June 2023 of the whole banking sector.
12/04/2024
የንግድ ስራ ገቢ
Ministry of Revenues of Ethiopia /የገቢዎች ሚኒስቴር /
የንግድ ስራ ገቢ የሚባለው፡-
1. ግብር ከፋዩ ዕቃዎችን በማስተላለፍ እና አገልግሎቶችን በመስጠት የሚያገኘውን የገንዘብ መጠን ጨምሮ በግብር ዓመቱ ከንግድ ስራ ያገኘው ጠቅላላ የገንዘብ መጠን፣
2. የንግድ ስራ ሃብትን በማስተላለፍ የሚገኝ የገንዘብ መጠን (ከመዝገብ ዋጋ በላይ ያለው ዋጋ)፣
3. በአዋጅ መሠረት የግብር ከፋዩ ገቢ ተደርገው የተወሰዱ ሌሎች ማናቸውም ገቢዎች፣
4. የካፒታል ንብረት የሆነን የንግድ ስራ ሃብት በማስተላለፍ በሚገኘው ጥቅም ላይ ሁለት ግብሮች ሊወሰኑ ይችላሉ፡፡
— የንግድ ትርፍ ግብር
— የካፒታል ዋጋ ዕድገት ግብር
5. ለንግድ ስራው ሃብት የተደረገው ወጪ ከንግድ ስራው ሀብት የተጣራ የመዝገብ ዋጋ የሚበልጠው የገንዘብ መጠን በንግድ ስራ ገቢ ውስጥ የሚካተት ሲሆን ከወጪው በላይ የሚገኘው ጥቅም ደግሞ የካፒታል ዋጋ ዕድገት ግብር ይከፈልበታል፡፡
04/04/2024
ግብር የሚከፈልበት የቤት ኪራይ ገቢ
ግብር የሚከፈልበት የኪራይ ገቢ የሚባለው በግብር ዓመቱ ግብር ከፋዩ ቤት በማከራየት ካገኘው ጠቅላላ ዓመታዊ ገቢ ላይ ለግብር ከፋዩ የተፈቀደው ጠቅላላ ወጪ ተቀናሽ ተደርጎ የሚቀረው ገቢ ላይ ነው፡፡
የተከራይ አከራዮች
• የተከራይ አከራይ በግብር ዓመቱ ያገኘው ግብር የሚከፈልበት ገቢ ነው የሚባለው የተከራይ አከራይ በግብር ዓመቱ ከተቀበለው ጠቅላላ የኪራይ ገቢ ላይ ለዋናው አከራይ የሚከፍለው ኪራይ እንዲሁም ገቢውን ለማግኘት ያወጣቸው ሌሎች ወጪዎች ከተቀነሱ በኋላ የሚቀረው ገንዘብ ነው፡፡
• ተከራይ የተከራየውን ቤት መልሶ እንዲያከራይ የሚፈቅድ የቤት ባለቤት ተከራዩ ግብሩን ሳይከፍል ቢቀር ስለእርሱ ሆኖ ግብሩን የመክፈል ኃላፊነት ይኖርበታል፡፡
Ministry of Revenues of Ethiopia /Ministry of Revenues of Ethiopia /የገቢዎች ሚኒስቴር / ሚኒስቴር /
04/04/2024
LOGO
የሰነደ ሙአለ ንዋይ ገበያ አዲስ መለያ ይፋ አደረገ።
Website (https://bit.ly/capital_site) | Facebook (https://bit.ly/capital_fb) | X (https://bit.ly/capital_X) | TikTok (https://bit.ly/Capital_tiktok) | Instagram (https://bit.ly/Capital_Insta) | Linkedin (https://bit.ly/Capital_In) | Youtube (https://bit.ly/capital_yt)
03/04/2024
The Reporter :
IMF talks end without agreement
A two-week round of discussions between Ethiopian officials and an International Monetary Fund (IMF) delegation in Addis Ababa has ended without a financial package deal, according to a statement from the Fund released yesterday.
IMF team led by Alvaro Piris “made substantial progress towards establishing how the IMF could support [Ethiopian] authorities’ economic program” between March 19 and April 2, 2024, but did not ink a staff level agreement, according to the statement.
IMF staff level agreement by the end of March was listed as a precondition by bilateral creditors when they approved a temporary debt payment suspension...
IMF Talks End Without Agreement | The Reporter | Latest Ethiopian News Today A two-week round of discussions between Ethiopian officials and an International Monetary Fund (IMF) delegation in Addis Ababa has ended without a financial
31/03/2024
Deloitte has acquired the first license for investment advisory services in the upcoming stock exchange more than a month after the Ethiopian Capital Market AuthorityEthiopian Capital Market Authority - የኢትዮጵያ የካፒታል ገበያ ባለስልጣንየኢትዮጵያ የካፒታል ገበያ ባለስልጣን (ECMA) first began offering licensure.
The Reporter
Deloitte Nabs Capital Market License | The Reporter | Latest Ethiopian News Today Deloitte has acquired the first license for investment advisory services in the upcoming stock exchange more than a month after the Ethiopian Capital Markets
29/03/2024
ዛሬ በሚጠናቀቀው የአክሲዎን ሽያጭ Amhara Bank አማራ ባንክ በሰነደ መዋእለ ንዋይ ገበያ (Securities Exchange) ላይ ከግል ኢንቨስተሮች ከፍተኛ ባለድርሻ የሚያረገውን አክሲዎን ገዛ።
አማራ ባንክ ከፍተኛውን መዋዕለ ነዋይ በመመደብ የ 10 በመቶ የአክሲዮን ድርሻ መግዛቱን ገልጿል።
ባንኩ የሰነደ መዋዕለ ገበያን ላይ በ 90.6 ሚሊዮን ብር ከፍተኛዉን ድርሻ የገዛ የግል ኩባንያ መሆን ችሏል። ይህን ተከትሎ የአክሲዮን ግዢን የመፈፀመ አምስተኛዉ ባንክ ሆኗል።
ካፒታል ገበያን በኢትዮጵያ ለማቋቋም ድርሻ ከገዙት ባንኮች ዉስጥ እስካሁን 308.1 ሚሊዮን ብር መሰብሰብ ተችሏል ።
Via- Capital
Commercial Bank of Ethiopia የኢትዮጵያ ንግድ ባንክ ከሰሞኑ በተፈጠረው የሲስተም ችግር ሳቢያ ከ 9 ሚሊዮን ብር በላይ የወሰዱትን ወደ 567 የሚጠጉ ግለሰቦችን ማግኘት አለመቻሉን አስታወቀ
ንግድ ባንክ ባጋጠመው የሲስተም ችግር ምክንያት ከተወሰደዉ ከ 801 ሚሊዮን ብር በላይ ገንዘብ 622 ሚሊዮን ያህሉን ወደ ባንኩ ተመላሽ ማድረጉን የገለፀዉ እና ቀሪ 567 ግለሰቦች ደግሞ የወሰዱትን 9.8 ሚሊዮን ብር ማግኘት አለመቻሉን አስታዉቋል።
መጋቢት 6 ቀን 2016 ዓ.ም. ምሽት ላይ ከ 3 ሰዓት ጀምሮ እስከ 8: 45 ድረስ ባለዉ 25 ሺህ 761 ደንበኞች ብር 801.4 ሚሊዮን መወሰዳቸውን ገልጿል።
ያልተገባ ጥቅም ለማግኘት በማሰብ በሂደቱ ዉስጥ የተሳተፉ 15 ሺህ ያህል የሂሳብ ቁጥሮችን ማግኘቱን ያስታወቀው ባንኩ 14 ግዜ ግበይት ነበራቸው ብሏል።
በዕለቱ 238 ሺህ 293 ግብይት መደረጉን እና አንድ የባንኩ ደንበኛ ከ 9 ጊዜ በላይ ግብይት መፈፀሙን የባንኩ ፕሬዚዳንት አቶ አቤ ሳኖ ለሁለተኛ ጊዜ በሰጡት መግለጫ አስታዉቀዋል።
በሂደቱ ላይ 57 በመቶ ተሳታፊ የነበሩት የዩኒቨርስቲ ተማሪዎች መሆናቸው ተነግሯል። አቶ አቤ ሳኖ እንደገለፁት እስከ ትላንት መጋቢት 16 ፤ 2016 ዓ.ም. ድረስ ከተወሰደዉ ገንዘብ 78 በመቶ ወይም ከ 622.9 ሚሊዮን ብር በላይ ወደ ባንኩ ተመላሽ ተደርጓል ብለዋል።
በተቀመጠው የጊዜ ገደብ ዉስጥ በፍቃደኝነት ገንዘብን ተመላሽ ያላደረጉ ግለሰቦች ስማቸዉን ጨምሮ ማንነታቸውን የሚገልፅ ምስዕል ከዛሬ ጀምሮ በተለያዩ አማራጮች ይፋ እንደሚያደርግ አስታዉቋል ።
Capital
18/03/2024
Addis International Bank 's (Addis Bank) profit for the fiscal year 2022/23 marked a departure from the Bank's previously strong growth trajectory, leaving it trailing behind its peers such as Enat, Global, and Berhan banks. The sharp decrease in a net profit of 223.4 million Br, recording a 35.2pc decline for the fiscal year 2022/23, has been largely attributed to a substantial reduction in foreign exchange income, shocking shareholders and sparking concerns over the Bank's strategic direction and operational efficiency.
Addis Fortune
Addis International Bank's (Addis Bank) profit for the fiscal year 2022/23 marked a departure from the Bank's previously strong growth trajectory, leaving it trailing behind its peers such as Enat, Global, and Berhan banks. The sharp decrease in a net profit of 223.4 million Br, recording a 35.2pc decline for the fiscal year 2022/23, has been largely attributed to a substantial reduction in foreign exchange income, shocking shareholders and sparking concerns over the Bank's strategic direction and operational efficiency.
READ MORE: https://ow.ly/3tLs50QVkpe
17/03/2024
ሕብረት ባንክ የኢትዮጵያ መዋዕለ ንዋይ ገበያ ባለድርሻ የሚያደርገውን የ50 ሚሊዮን ብር አክሲዮን ድርሻ ገዛ!
**********
ኅብረት ባንክ በቅርቡ ወደ ሥራ ይገባል ተብሎ በሚጠበቀው የኢትዮጵያ መዋዕለ ንዋይ ገበያ አክሲዮን ማኅበር ላይ 50 ሚሊዮን ብር የሚያወጡ አክሲዮኖችን በመግዛት የኩባንያው ባለድርሻ ሆነ።
በኢትዮጵያ መዋዕለ ንዋይ ገበያ አክሲዮን ማኅበርና በኅብረት ባንክ መካከል በተደረሰው ስምምነት መሠረት ኅብረት ባንክ የገዛው የ50 ሚሊዮን ብር አክሲዮን በኩባንያው ውስጥ የአምስት በመቶ ባለድርሻ የሚያደርው መሆኑም ታውቋል፡፡
ይህ ስምምነት ከኢትዮጵያ መዋዕለ ንዋይ ገበያ አክሲዮን ማኅበር ላይ አክሲዮኖችን የገዙ ባንኮችን ቁጥር ከፍ ያደረገው ሲሆን፣ እስካሁን አክሲዮን መግዛታቸውን በይፋ ያሳወቁት ዘመን ባንክ፣ ስንቄ ባንክ፣ አዋሽ ባንክና ግሎባል ባንክ ሲሆኑ፣ ሌሎች ባንኮችም መጠኑ አነስተኛ ይሁን እንጂ አክሲዮኖችን ከኩባንያው ገዝተዋል፡፡
ከኢትዮጵያ መዋዕለ ንዋይ ገበያ አክሲዮን ማኅበር አክሲዮን መግዛታቸውን ያሳወቁት አራቱ ባንኮች አዋሽ፣ ኅብረት፣ ግሎባል ባንክ ኢትዮጵያ የ220 ሚሊዮን ብር አክሲዮን መግዛታቸውን ያመላክታል፡፡
ከመዋዕለ ንዋይ ገበያ አክሲዮን ማኅበር የተገኘው መረጃ እንደሚያመለክተው፣ እስካሁን ካከሄደው የአክሲዮን ሽያጭ ማሰባሰብ የቻለው ካፒታል መጠን ከዕቅዱ በላይ ሊሆን እንደሚችል ተጠቁሟል፡፡
አጠቃላይ የአክሲዮን ሽያጩን ለማካሄድ ያስቀመጠው ቀነ ገደብ ማርች 30 ቀን የሚጠናቀቅ ሲሆን፣ በቀረበው ሁለት ሳምንታት ተጨማሪ አዲስ ኩባንያዎች ይንቀሳቀሳሉ ተብሎ እየተጠበቀ ይገኛል፡፡
በኢትዮጵያ የካፒታል ገበያ መፈጠርን ተከትሎ የሚቋቋመው ይህ ኩባንያ፣ ለተለያዩ የኢንቨስትመንት መስኮች የኢንቨስትመንት ፈንድ ለማሰባሰብና ሌሎች ዘመናዊ የግብይቶችን ለማካሄድ ከፍተኛ ጠቀሜታ ያለው ተብሎ የሚታመንበት ነው፡፡ ኩባንያ መፈጠር በፋይናንስ ዘርፍ ውስጥ ተጨማሪ የቢዝነስ እንቅስቃሴዎች እንደሚካሄዱ ያስችላል ተብሎም ይጠበቃል፡፡
በኢትዮጵያ መዋዕለ ንዋይ ገበያ አክሲዮን ማኅበርን በኅብረት ባንክ መካከል የተፈጸመውን የአክሲዮን ግዥ ኅብረት ባንክን በመወከል የፈረሙት የባንኩ ፕሬዚዳንት አቶ መላኩ ከበደ ናቸው፡፡
የኢትዮጵያ መዋዕለ ንዋይ ገበያ በኩል ደግም ዋና ሥራ አስፈጻሚ ጥላሁን እስማኤል (ዶ/ር) ናቸው፡፡ ኅብረት ባንክ በኢትዮጵያ የባንክ ኢንዱስትሪ ውስጥ ከ20 ዓመታት በላይ የቆየ የግል ባንክ ነው፡፡ የ2015 የሒሳብ ዓመት ዓመታዊ ሪፖርቱ እንደሚያመለክተው፣ አጠቃላይ የሀብት መጠኑ ከ82.5 ቢሊዮን ብር በላይ ደርሷል፡፡ በዚሁ የሒሳብ ዓመት አጠቃላይ የካፒታል መጠኑ 9.4 ቢሊዮን ብር ሲሆን፣ ከታክስ በፊት 3.06 ቢሊዮን ብር ማትረፉ መገለጹ አይዘነጋም፡፡
የተቀማጭ ገንዘብ መጠኑም 64.5 ቢሊዮን ብር ሲሆን፣ በዚሁ በ2015 የሒሳብ ዓመት መጨረሻ ላይ የብድር ክምችት መጠኑ 60.1 ቢሊዮን ብር ነበር፡፡
By #ሪፖርተር
#ሕብረት #ባንክ
Ethiopian Stock Market Dealer
The Reporter
Hibret Bank
12/03/2024
የግብር ከፋይ ደረጃዎች
መጋቢት 03/2016 ዓ.ም (የገቢዎች ሚኒስቴር)
Ministry of Revenues of Ethiopia /Ministry of Revenues of Ethiopia /የገቢዎች ሚኒስቴር / ሚኒስቴር /
በፌዴራል የገቢ ግብር አዋጅ ቁጥር 979/2008 መሠረት፡-
የደረጃ "ሀ" ግብር ከፋይ
👉 የደረጃ "ሀ" ግብር ከፋይ የሚባለው ድርጅት ወይም ጠቅላላ ዓመታዊ ገቢው ብር አንድ ሚሊዮን ወይም ከዚህ በላይ የሆነ ማንኛውም ሌላ ሰው፤
የደረጃ "ለ" ግብር ከፋይ
👉 የደረጃ "ለ" ግብር ከፋይ የሚባለው ድርጅትን ሳይጨምር ዓመታዊ ጠቅላላ ገቢው ከብር አንድ ሚሊዮን ብር የሚያንስ ነገር ግን ብር አምስት መቶ ሺ ብር እና ከዚያ በላይ የሆነ፤
የደረጃ "ሐ" ግብር ከፋይ
👉 ደረጃ "ሐ" ግብር ከፋይ የሚባለው ድርጅትን ሳይጨምር ዓመታዊ ጠቅላላ ገቢው ከብር አምስት መቶ ሺ ብር የሚያንስ ሰው ሲሆን የታክስ ባለሥልጣኑ ታክስ ከፋዩ የሚያሳውቀውን ግብር ወይም የሚያገኘውን ሌላ መረጃ መሠረት በማድረግ ለግብር ዓመቱ የግብር ከፋዩ ደረጃ የተለወጠ መሆን አለመሆኑን ይወስናል፡፡
ሚኒስትሩ በዚህ አንቀጽ ንዑስ አንቀጽ (1) የተመለከተውንና ግብር ከፋዮችን የደረጃ "ሀ"፣ የደረጃ "ለ" ወይም የደረጃ "ሐ" ግብር ከፋይ ብሎ ለመመደብ የሚያስችለውን ዓመታዊ ጠቅላላ የገቢ መጠን በኢኮኖሚ ጥናት ላይ በመመስረት ቢያንስ በአምስት ዓመት ጊዜ ውስጥ ማሻሻል አለበት/ያሻሽላል፡፡
Click here to claim your Sponsored Listing.
Category
Contact the business
Telephone
Address
Addis Ababa