EthioTimes
EthioTimes is a source of credible news and entertaining TV and radio productions.
05/31/2026
"ስንሰጥ በደስታ ይሁን" ብፁዕ አቡነ ዮሴፍ
ብፁዕ አቡነ ዮሴፍ የሲዳማ እና ጌዲዮ ሀገረ ስብከት ሊቀ ጳጳስ በመቄዶንያ የምስጋና እና ማዕድ ማጋራት ፕሮግራም ላይ ተገኝተዉ እንደተናገሩት መስጠት የሚጀምረዉ ራስን ከመስጠት ሲሆን ራሱን ለእግዚአብሔር የሰጠ ቁሳቁስ ወይም ገንዘብ ለመስጠት አይቸገርም፡፡
👉ስጦታ ከዉስጥ የመነጨ ፣ በሀይማኖት የፀና ፣ ርህራሄ የተሞላበት ፣ በመንፈሳዊነት የተቃኘ ፣ እንዲሁም የሌሎችን ችግር ፣ ህመም ፣ ረሀብ እና ጥም መጋራት ሲሆን ከዉስጥ የመነጨ ደስታን ይሰጠናል በማለት የመስጠትን ጥልቅ ሚስጥር ገልፀዉልናል፡፡
👉ብፁዕነታቸዉ ለመቄዶንያ ያደረጉት ድጋፍ ሊበረታታ የሚገባዉ አርዓያ እና አስተማሪ የሆነ ተግባር መሆኑን ገልፀዉ ሁላችንም ከዚህ መልካም ተግባር አርዓያነትን ወስደን የቻልነዉን ሁሉ ለመቄዶንያ ድጋፍ እናድርግ ፣ መቄዶንያን እናግዝ ብለዉናል!!
👉በመጨረሻም በዚህ የምስጋና እና የማዕድ ማጋራት ፕሮግራም ላይ በመገኘታቸዉ የተሰማቸዉን ጥልቅ የሆነ ደስታ ገልፀዋል!!
አይነ ስዉራን የተፈወሱበት የቅ/ጊዮርጊስ ቤተክርስቲያን‼️
+++++++++++++++++++++++++++
በቪዲዮዉ የሚታየዉ የቅ/ጊዮርጊስ ቤተክርስቲያን ፀበሉ አይነ ስዉራን የሚፈወሱበት ተአምራዊ ፀበል መገኛ እንደሆነ ሰማዕቱም ስለት ሰሚ መሆናቸዉን አባቶች ምስክርነታቸዉን ሰጥተዋል። በአሁኑ ሰአትም ቤተክርስቲያኑ ግንባታ ላይ ስለሆነ በመላዉ አለም ያላችሁ ወገኖቻችን የአቅማችሁን ታግዙን ዘንድ በእግዚአብሔር ስም እንማፀናለን በማለትም አባቶች ጥሪያቸዉን አሰምተዋልና የምንችለውን በማገዝ የበረከቱ ተካፋይ እንሁን።
ድጋፍ ለማድረግ የቤክርስቲያኑ አካዉንት
👇👇👇
ንግድ ባንክ- 1000292743258 (ጋይታ ጊዮርጊስ)
ስልክ- 0923418637
ለብዙዎች እንዲዳረስ እባካችሁ ሼር አድርጉት‼️
05/31/2026
05/31/2026
አትሌት ደራርቱ ቱሉ ልጇን ዳረች‼️
ጀግናዋ አትሌት ደራርቱ ቱሉ ወንድ ልጇን ተስፋዬ ፀጋውን ትናንት ድራለች ። የረዳት ኮሚሽነር ደራርቱ ቱሉ ልጅ
ኢንጅነር ተስፋዬ ፀጋው ከገብሬላ ተስፋዬ ጋር ነዉ የተሞሸረዉ።
ተስፋዬ ከአሜሪካው ፍሎሪዳ ዩኒቨርሲቲ በኢንጅነሪግ በከፍተኛ ማዕረግ የተመረቀ ሲሆን፤ ከተመረቀም በኋለ በኢትዮጵያ የረ/ኮ ደራርቱ ቱሉ ድርጅት ውስጥ ጠቅላላ ስራ አስኪጅ ሆኖ እንያገለገለ ይገኛል።
Via- maleda
05/30/2026
በመጨረሻ በአውሮፓ ሻምፒዮንስ ሊግ የፍጻሜ ጨዋታ ፒኤስጂ አርሴናልን በፍጹም መለያ ምት በማሸነፍ የዋንጫ ባለቤት መሆን ችሏል።
የልደታ ለማርያም የገጠር ገዳምን እንርዳ‼️
+++++++++++++++++++++++++++
እነሆ በጎንደር ጃናሞራ በምትገኘዉ በጥንታዊቷ የልደታ ማርያም አንድነት ገዳም የሚገኙ ገዳማዊያን አባቶችና እናቶች በድርቅ ፣ በመሬት ናዳና በጎርፍ ምክንያት ችግር ላይ ወድቀዉ የሚቀምሱት የሚለብሱት የሚጠለሉበት አጥተዋል። ቤተክርስቲያኗም አደጋ ላይ ስለሆነች ለእድሳት የአቅማችሁን አግዙን በማለት የበረከቱ ተሳታፊ እንሆን ዘንድ መነኮሳቱ የአደራ ጥሪ አቅርበዋል።
ድጋፍ ለማድረግ👇👇👇
ንግድ ባንክ- 1000423896047
አማራ ባንክ- 9900023686523
አባይ ባንክ- 4881117054385011
ስልክ- 0902269763/ 0992106771
ለብዙዎች እንዲዳረስ እባካችሁ ሼር አድርጉት‼️
05/30/2026
የማያድን ፍቅር‼️
(ሙሉቃል እንደጻፈው)
"ሃገር እንዳይጠፋ ትውልድም ከጥፋት እንዲጠበቅ መመኘትና መጣር ምስጋናና ሽልማት የማይሻ የእያንዳንዳችን ግዴታ ነው። ነውር ቀስ በቀስ እንዳይላመደን ፣ በዘመናት ውስጥ እንደ ሃገር የተፀየፍነው ነውር ቀስ ብሎ እንዳይከበን በመጠንቀቃችን ውስጥ አንዳች ጥፋት የለም! ይህ ሁሉ ጥንቃቄና የእምነት አጥር ደሞ የስው ልጆችን ሁሉ ከጥፋት ለማዳን ነው!
በዚህ ምስኪን ልጅ ታሪክ ውስጥ ግን ሃገርና ትውልድን ከማዳን ቀና መንፈስ ይልቅ ይህ ነው ተብሎ የማይገለፅ የገንዘብ ፍቅርና የሰውን ልጅ ገንድሶ የመክበር ስግብግብነት ጎልቶ ይታየኛል!
ሰው ሁሉ እንዳይወድቅ የደገፈው የራሱ ማስተዋል አይደለም! ሁላችን የቆምነው በእግዚአብሔር ፀጋና ምህረት ነው። እንዲድን የፈለግነው ሌሎችንም ይዞ እንዳይጠፋ የሰጋነው ሰው በዙሪያችን ቢኖር የመመለሻ የመምከሪያና የማስተማሪያ መንገዳችን ሁሉ ፍቅር እንዳይጎለው መጠንቀቅ ያስፈልጋል!
ልጆቻችሁ ፣ ወንድሞቻችሁ ፣ እህቶቻችሁ ፣ ከስጋችሁ አንደኛው አካል በዚህ አስከፊ ጥፋት ቢወድቁባችሁ ልትሄዱ የምትችሉበትን የፍቅርና የርህራሄ መንገድ ሁሉ ለሌሎችም መስጠት የሚያድነው ሃያል ፍቅር ነው!
የነጋዴዎች ፣ የውሸታሞች ፣ የግብዞች መንገድ ግን ከሆዳቸው ጋር ነው! የተሻለ ገንዘብ ከቀረበላቸው ተፀየነፍነው ላሉት ነውር ማጎንበሳቸው
የሚቀር አይመስለኝም!
በስተመጨረሻ ፍቅር የሌለበት ነገር ሁሉ ከንቱ የሚሆን ይመስለኛል! ስለዚህ ነገር ከፃፋችሁም ሆነ ከተናገራችሁ በፍቅር ይሁን! በርህራሄ ይሁን! እናቱን እናታችሁ ፣ እህቱን እህታችሁ አድርጉ!
እንኳን ሰባሪው ቃላችን የእዝነት ቃላችን ሳይቀር በደሉን እንዳያስታውሰው እንጣር‼️
ፍቅር የበለጠውን ስራ ይሰራልና‼️"
05/30/2026
የአርሰናል እና ፒኤስጂ ጨዋታ በመደበኛው የጨዋታ ክፍለጊዜ 1ለ1 ተጠናቆ ወደ ተጨማሪ ሰላሳ ደቂቃ አምርቷል።
05/30/2026
የቀድሞ የአርሰናል ኮከብ ቴሪ ዳንኤል ኦነሪ አሁን በአርሰናል እና ፒኤስጂ ጨዋታ ላይ።
👉 በመጀመሪያው 45 ደቂቃ ላይ አርሰናል 1 ለ 0 እየመራ ይገኛል።
Click here to claim your Sponsored Listing.
Category
Contact the business
Website
Address
Opening Hours
| Monday | 9am - 5pm |
| Tuesday | 9am - 5pm |
| Wednesday | 9am - 5pm |
| Thursday | 9am - 5pm |
| Friday | 9am - 5pm |
| Saturday | 9am - 5pm |
| Sunday | 9am - 5pm |