EthioTimes

EthioTimes

Share

EthioTimes is a source of credible news and entertaining TV and radio productions.

06/23/2026

ክርስቲያኖ ሮናልዶ አዲስ ታሪክ ጻፈ‼️

ክሪስቲያኖ በ ስድስት የተለያዩ የዓለም ዋንጫዎች ላይ ግብ በማስቆጠር በታሪክ የመጀመሪያው ተጫዋች መሆን ችሏል።

​ከሁለት አስርት ዓመታት በፊት (በ2006) የጀመረውን ተከታታይ የዓለም ዋንጫዎች የማስቆጠር ጉዞ በመቀጠል፣ በዓለም መድረክ ላይ ያለውን አስደናቂ ጥንካሬ እና ዘላቂነት አስመስክሯል።

​የታሪካዊው የስድስት ዓለም ዋንጫዎች ጉዞ
👉​2006: ጀርመን
👉​2010: ደቡብ አፍሪካ
👉​2014: ብራዚል
👉​2018: ሩሲያ
👉​2022: ኳታር
👉​2026: አሜሪካ፣ ሜክሲኮ እና ካናዳ

06/23/2026

አስቸኳይ‼️

አባቶች አንገታቸዉን ደፉ‼️

ገዳሙ ከመበተኑ በፊት እንድረስ‼️

በወሎ የሚገኘዉ የኤፍራታ ቅድስት ልደታ ማርያም ፤ ዮሀንስ ወልደነጎድጓድ እና አቡነ ዘርአቡሩክ አንድነት ገዳም መነኮሳዉያን አባቶችና እናቶች ሚበሉት ሚጠጡት ሚለብሱት ሚጠለሉበት እስከማጣት እንዲሁም ቤተክርስቲያኑ እያፈሰሰባቸዉ በመቸገራቸዉ በመላዉ አለም ላላችሁ ደጋጎች ከታች ባለዉ አካዉንት የምንችለዉን በማገዝ የበረከቱ ተሳታፊ እንድንሆን ጥሪ መነኮሳቱ አቅርበዋል።

ድጋፍ ለማድረግ

👇👇👇

ንግድ ባንክ- 1000201267114

አቢሲኒያ- 240499045

ኪዳነ ምህረት የልባችሁን መሻት ትፈፅምላችሁ‼️

06/23/2026

ኢትዮጵያዊው Content Creator አቤል ብርሀኑ
ከተባበሩት አረብ ኤምሬትስ የ10 ዓመት የጎልደን ቪዛ ተበርክቶለታል።

​እንኳን ደስ አለህ‼️

06/23/2026

Exit Exam የወሰዳችሁ ተማሪዎች
👇👇👇

ከሰኔ 04-12/2018 ዓ.ም የተሰጠው የ2018 ዓ.ም የከፍተኛ ትምህርት የመውጫ ፈተና (Exit Exam) ውጤት ይፋ ተደረገ።

ተፈታኞች የመውጫ ፈተና ውጤታቸውን በ https://result.ethernet.edu.et ላይ በመግባት መመልከት ይችላሉ።

መጀመሪያ የተቀመጠውን ሊንክ ይጫኑ በመቀጠል 'Exit Examination' ላይ 'View Results' የሚለውን በመጫንና Username በማስገባት ውጤት መመልከት ይቻላል።

Via- Tikvahethiopia

06/23/2026

በወንጀል ተከሶ ከእስራት በወጣ በ3ኛው ቀን በስርቆት ወንጀል ድጋሚ ታሰረ‼️

ዳዊት በላቸው የተባለው ተከሳሽ ከዚህ ቀደም የቅሚያ ወንጀሉን የፈፀመው በኮልፌ ቀራንዮ ክፍለ ከተማ ወረዳ 8 ልዩ ቦታው አረንጓዴ ሰፈር ተብሎ ከሚጠራው አካባቢ ሰኔ 7 ቀን 2014 ዓ/ም ነበር።

ግለሰቡ የዋጋ ግምቱ 25 ሺህ ብር የሚያወጣ ሳምሰንግ M 32 ሞባይል ከግል ተበዳይ ላይ ቀምቶ ለማምለጥ ሲሞክር በፖሊስ አባላትና በህብረተሰቡ ትብብር እጅ ከፈንጅ ተይዞ አስፈላጊውን ምርመራ ከተጣራበት በኋላ አቃቤ ህግ ክስ መስርቶበት ጉዳዩን የተመለከተው የፌዴራል የመጀመሪያ ደረጃ ፍርድ ቤት ኮልፌ ቀራንዮ ምድብ ወንጀል ችሎት በ3 አመት ፅኑ እስራት እንዲቀጣ ውሳኔ አስተላልፎበት በማረሚያ ቤት መቆየቱን በክፍለ ከተማው ፖሊስ ዋና መምሪያ የቤተል አካባቢ ፖሊስ መምሪያ አስታውቋል።

የ3 አመት የእስር ጊዜውን ጨርሶ ከማረሚያ ቤት የወጣውና ያልታረመው ይህ ግለሰብ በወጣ በ3ኛው ቀን በኮልፌ ቀራንዮ ክፍለ ከተማ ወረዳ 6 ቤተል አካባቢ ከሚገኝ አንድ አፖርታማ ገብቶ 19 ሺህ ብር የሚገመቱ የተለያዩ ጫማዎችን ሰርቆ ለማምለጥ ሲሞክር ስራ ላይ በነበሩ የወንጀል መከላከል የፖሊስ አባላትና በህብረተሰቡ ትብብር እጅ ከፈንጅ መያዙን የቤተል አካባቢ ፖሊስ መምሪያ ገልጿል።

የተሰረቁት ንብረቶች በኤግዚቢት ተይዘው በግለሰቡ ላይ አስፈላጊው ምርመራ ከተጣራበት በኋላ አቃቤ ህግ ክስ መስርቶበታል፤ ጉዳዩን የተመለከተው የፌደራል መጀመሪያ ደረጃ ፍርድ ቤት ኮልፌ ቀራንዮ ምድብ ፈጣን ወንጀል ችሎት ተከሳሹን ያስተምራል ሌሎች ወንጀል ፈፃሚዎችን ያስጠነቅቃል በማለት ሰኔ 16 ቀን 2018 ዓ/ም በዋለው ችሎት በፈፀመው ደጋጋሚ የወንጀል ድርጊት በ4 አመት ከ5 ወር ፅኑ እስራት እንዲቀጣ ውሳኔ እንዳስተላለፈበት ፖሊስ ጠቅሷል፡፡

አብዛኛው ወንጀል ፈፃሚ በማረሚያ ቤት የእስር ቆይታው በጥሩ ስነ ምግባር ታርሞና ታንፆ ወደ ማህበረሰቡ ቢቀላቀልም አንዳንድ የእጅ አመል ያለባቸው ግለሰቦች ደግሞ ከማረሚያ ቤት ወጥተው ወንጀል ቢፈጽሙም ከህግ እንደማያመልጡ የገለፀው የአዲስ አበባ ፖሊስ ዋና ጠቅላይ መምሪያ ህብረተሰቡ ወንጀል እንዳይፈፀምበት ተገቢውን ጥንቃቄ በማድረግ ለፀጥታ አካላት ጥቆማ ከመስጠት ጀምሮ የሚያደርገውን ትብብር አጠናክሮ እንዲቀጥል ጥሪውን አቅርቧል።

Via- አዲስ አበባ ፖሊስ

06/23/2026

ለንግድዎ፣ ለቤተሰብዎ እና ለኢንቨስትመንትዎ ፍጹም ምርጫ — በሳር ቤት / ቡልጋሪያ!

የአፍሪካ ህብረት አቅራቢያ በሚገኘው ስትራቴጂካዊና ተፈላጊ ስፍራ በሆነው ሳር ቤት (ቡልጋሪያ ሳይት) ዘመናዊ የንግድ ሱቆችን እና ምቹ የመኖሪያ አፓርታማዎችን በተለያዩ የካሬ አማራጮች እያቀረብን ነው።

የንግድ ሱቆች (Commercial Shops)
የካሬ አማራጭ፦ ከ25 ካሬ እስከ 75 ካሬ

ተመራጭ ለ፦
• ፋርማሲ
• ሬስቶራንት
• ባንክ
• የተለያዩ የንግድ ተቋማት

የመኖሪያ አፓርታማዎች (Apartments)
የካሬ አማራጮች፦
ካሬ አማራጭ ቅድመ ክፍያ
• 81 ካሬ =727,128
• 111 ካሬ =996,435
• 134 ካሬ =1,202,904168 ካሬ = 1, 508,119
• 182 ካሬ =1, 633,795

ቀላል የክፍያ ስርዓት በ10% ቅድመ ክፍያ ብቻ የቤት ባለቤት ይሁኑ!

እጅግ ተመጣጣኝ ዋጋዎች እና ልዩ የክፍያ አማራጮች ተዘጋጅተዋል።

ማሳሰቢያ
ይህ ልዩ የዋጋ ቅናሽ የተዘጋጀው ለውስን ቤቶች ብቻ ነው። እድሉን እንዳያመልጥዎ አሁኑኑ ይደውሉ!

📞 +251-983-79-6622

06/23/2026

አስቸኳይ የበረከት ጥሪ‼️

በሰሜን ጎንደር ደባርቅ አካባቢ የሚገኘዉ የኪኖ ኪዳነምህረት ቤተክርስቲያን ለረዥም አመታት ግንባታ ላይ ቢሆንም በአሁኑ ሰአት በገንዘብ ችግር ቤተክርስቲያኑ ሙሉ በሙሉ ከመሰራት ቆሟል። ስለሆነም ቤተክርስቲያኑን ለማሰራት አባቶች በእግዚአብሔር ስም ጥሪ አቅርበዋልና የበረከቱ ተሳታፊ እንሁን።

ድጋፍ ለማድረግ

👇

ንግድ ባንክ- 1000201850021

አቢሲኒያ- 255527077

አባይ- 2361119451656012

Photos from EthioTimes's post 06/23/2026

በዛሬዉ እለት ከስምንት አመታት በፊት‼️

Photos from EthioTimes's post 06/23/2026

በኢትዮጵያ የስፖርት ዘርፍ አዲስ ምዕራፍ ሊከፍት የሚችል የመጀመሪያው አገር አቀፍ የስፖርት ኤግዚቢሽን ሊካሄድ ነው‼️

በኢትዮጵያ የስፖርት ዘርፍ ታሪክ አዲስ የኢንዱስትሪ ዕንቅስቃሴ ለመጀመር እና ስፖርትን ከመዝናኛነት ወደ ላቀ የኢኮኖሚ ምንጭነት ለማሸጋገር ያለመ ታላቅ አገር አቀፍ የስፖርት ኤግዚቢሽን በአዲስ አበባ ሊካሄድ መሆኑ ተገለጸ።

ይህንን በአገሪቱ ለመጀመሪያ ጊዜ የሚካሄደውን ታላቅ ኹነት ያዘጋጁት አዱሊያን ማስታወቂያ እና ዳይመንድ ማርኬቲንግ ኤንድ ኮሚኒኬሽን ሲሆኑ፣ ዝግጅቱ የኢትዮጵያን ስፖርት ከባሕላዊ የሩጫ እና የእግር ኳስ ማዕቀፍ አውጥቶ ወደ ዘመናዊ የቴክኖሎጂ አጠቃቀም፣ የንግድ ትስስር እና የኢንዱስትሪ ምርታማነት የሚያሸጋግር የለውጥ ምዕራፍ እንደሚሆን አዘጋጆቹ በሰጡት ጋዜጣዊ መግለጫ አስታውቀዋል።

ይህ አውደ ርዕይ እና አገራዊ መድረክ በርካታ ዘርፈ ብዙ ፋይዳዎችን ይዞ የሚቀርብ ሲሆን፣ የስፖርት ዕቃ አምራቾችን፣ አከፋፋዮችን፣ ስፖርተኞችን እና የስፖርት ማሕበራትን በአንድ መድረክ በማገናኘት የአገር ውስጥ ምርትን ማበረታታት እና የገበያ ትስስር መፍጠር፤ በዓለም ላይ ያሉ ዘመናዊ የስፖርት ስልጠና ቴክኖሎጂዎችን (Digital Sports Solutions)፣ የስፖርት ሕክምና፣ አመጋገብ እና ሳይንስ ላይ ያተኮሩ የውይይት መድረኮችን ለኢትዮጵያ ስፖርተኞችና አሰልጣኞች ማስተዋወቅ፤ ወጣቶች እና ቤተሰቦች በአካል ተገኝተው የተለያዩ የስፖርት አይነቶችን እንዲሞክሩ በማድረግ፣ በአካላዊ ብቃት፣ በእንቅስቃሴ እና በጤናማ የአኗኗር ዘይቤ ላይ ሰፊ ግንዛቤ መፍጠር እንዲሁም የስፖርት ዝግጅቶችን በንግድ መልክ በማደራጀት ለሀገር ውስጥ አምራቾች ሰፊ እድል መስጠት፤ ይህም የውጭ ምንዛሪ ወጪን በመቀነስ የአገር ውስጥ አቅምን ለመገንባት እና ለዜጎች የስራ ዕድል ለመፍጠር ከፍተኛ አስተዋጽዖ ይኖረዋል።

# # # ለሀገር የሚሰጠው ስልታዊ ጠቀሜታ

ኢትዮጵያ በዓለም አቀፍ ደረጃ በስፖርቱ መስክ የጎላ ዝና ያላት ቢሆንም፣ ይህንን እውቅና ወደ ስፖርት ኢንዱስትሪ ለመቀየር የሚያስችል የተቀናጀ የንግድ እና የልውውጥ መድረክ ክፍተት እንደነበረበት ይነገራል። ዳይመንድ ማርኬቲንግ እና አዱሊያን ማስታወቂያ ይህንን ክፍተት በመሙላት የኢትዮጵያን ስፖርት ከ"ሞያ" ወደ "ኢንዱስትሪ" ለማሸጋገር አቅኚ የለውጥ ስራ መጀመራቸውን ገልጸዋል።

በተጨማሪም ዝግጅቱ ከፍተኛ ጥራት ያላቸውን (MDF-based) የኤግዚቢሽን ስታንዳርዶችን የሚጠቀም በመሆኑ፣ ለወደፊት በሀገሪቱ ለሚካሄዱ ስፖርታዊ ኹነቶች አዲስ የጥራት ደረጃ (Benchmark) ያስቀምጣል። ይህም ኢትዮጵያን በዓለም አቀፍ ደረጃ በስፖርት አስተናጋጅነት (Sports Event Hub) እንድትታወቅ በማድረግ ረገድ ለስፖርት ዲፕሎማሲው ትልቅ አጋዥ እንደሚሆን ታምኖበታል።

ኩባንያዎቹ ከዚህ ቀደም መሰል ዝግጅቶችን የማካሄድ ልምድ እንዳላቸው የገለጹ ሲሆን፣ ከአዲስ አበባ ወጣቶች ማሕበር ጋር በመተባበር "የአመለካከት እና አስተሳሰብ ለውጥ ኤግዚቢሽን" እንዲሁም ከአዲስ አበባ ስፖርት ኮሚሽን ጋር በመተባበር በጃን ሜዳ "የባሕል እና ስፖርት ፌስቲቫል" በተሳካ ሁኔታ ማከናወናቸውን አስታውሰዋል።

ለተሳታፊዎች እና ለጎብኚዎች ደህንነት ከፍተኛ ትኩረት የተሰጠው ሲሆን፣ እያንዳንዱ የኤግዚቢሽን ቦታ (Zone) በዓለም አቀፍ የደሕንነት መመዘኛዎች መሰረት እንደሚዋቀር ተገልጿል። ለዚህም ይረዳ ዘንድ ከፌዴሬሽኖች፣ ከጤና ባለሞያዎች እና ከሚመለከታቸው የደህንነት አካላት ጋር በቅርበት በመስራት ላይ መሆናቸውንና የህክምና እና የድንገተኛ አደጋ ዝግጅቶች በተሟላ ሁኔታ እንደሚቀርቡ አዘጋጆቹ አረጋግጠዋል።

ይህ አገር አቀፍ የስፖርት ኤግዚቢሽን የአንድ ጊዜ ክስተት ብቻ ሆኖ እንደማይቀረና ዋና ዓላማው በየዓመቱ የሚካሄድ ብሔራዊ የስፖርት ክብረ በዓል (Annual Sports Exhibition) ማድረግ መሆኑ ተገልጿል። የዘንድሮውን የመጀመሪያ ዝግጅት ስኬት እንደ ግብዓት በመጠቀም፣ በቀጣይ ዓመታት የክልል እና የዓለም አቀፍ ተሳታፊዎችን በማካተት ዝግጅቱን ይበልጥ ለማስፋት ታቅዷል።

Photos from EthioTimes's post 06/23/2026

"ድህነት ፈሪ ያደርጋል‼️" አርቲስት ዳንኤል አሸናፊ (ዳኒ ጢሞ)

በንጉስ አርማ ቲያትር አዳራሽ ውስጥ በተደረገው የገቢ ማሰባሰቢያ ፕሮግራም ላይ ፣ ዳኒ ጢሞ መላው የኢትዮጵያን ህዝብ እና የጥበብ ሰዎችን ልብ የነካ፣ የብዙዎችንም ልብ የነካ እጅግ አስገራሚ እና ጥልቅ ንግግር አድርጓል።

ዳኒ በመልዕክቱ "ማጣት እና ድህነት፤ መራብ፣ መጠማት ወይም አለመልበስ ብቻ አይደለም። ከዛ በላይ ስነ-ልቦናን ሰብሮ ሰውን ፈሪ ያደርጋል ሲል የችግሩን አስከፊነት እና የሰውን ልጅ ስነ-ልቦናዊ ስብራት ገልፆል።"

Photo Credit- Merawi Production

Want your business to be the top-listed Media Company in Silver Spring?
Click here to claim your Sponsored Listing.

Address

Silver Spring, MD

Opening Hours

Monday 9am - 5pm
Tuesday 9am - 5pm
Wednesday 9am - 5pm
Thursday 9am - 5pm
Friday 9am - 5pm
Saturday 9am - 5pm
Sunday 9am - 5pm