Hanan Mohammed
It has always been my dream to see Ethiopia🇪🇹 flourish.
08/06/2026
ዛሬ ማምሻውን ምሽት 12:00 በጋምቤላ ከተማ በአንድ የፌዴራል ፖሊስ አባል አማካኝነት ተከስቶ የነበረው ያልተጠበቀ የተኩስ ልዉዉጥ የነበረ መሆኑን አንድ ከፍተኛ የጋምቤላ ክልል ከፍተኛ ባለስልጣን ማምሻዉን አሳዉቀዉኛል።
አባሉ በአሁኑ ሰዐት በከበባ ዉስጥ ያለ እና ተጨማሪ ዉድመት እንዳያስከትል በቁጥጥር ስር መኖሩን የመረጃ ምንጮቼ ገልፀዉልኛል።
ክስተቱ ከተቀሰቀሰ በኋላ የክልሉና የፌዴራል ፀጥታ አካላት በቅንጅት ባደረጉት ፈጣን እንቅስቃሴ ሁኔታው ወደ ከፋ ደረጃ እንዳይሸጋገር ማድረግ ተችሏል።
የክልሉ መንግሥት ከጉዳዩ ጋር ተያይዘው ያሉ ዝርዝር ምክንያቶች በሕግና በሥርዓት ተጣርተው ተገቢው እርምጃ እንደሚወሰድ ያረጋገጠ ሲሆን፣ የፀጥታ አካላትም አስፈላጊውን የጥበቃና የክትትል ሥራ በቀጣይነት እንደሚያከናውኑ አስታውቋል።
ሰላም ለጋምቤላ!!
ቻይና አብዲ
30/05/2026
አራዳ ፓርክ
15/05/2026
#ከተባለልህ መድረስህ አይቀርም!
#ይህ ፎቶሾፕ ወይ AIይም እንዳይመስልህ።እውነተኛ ፎቶ ነው።
ዲና ሲቦማና አሁን 18 ዓመቱ ነው። የ 6 ዓመት ህፃን እያለ በኮንጎ(DRC) ብሄራዊ ፓርክ ለመጎብኘት ከወንድምና ከአክስቱ ልጅ ጋር ተገኘ።ቀኑን ግን እንዳሰቡት ሚዝናኑበት ሳይሆን ቀረ።ከኬጁ ያመለጠ ቺምፓንዚ ሶስቱ ላይ ጥቃት ሰነዘረ በዚህም ወንድሙና የኣክስቱ ልጅ ሲሞቱ እሱ ክፉኛ ተጎድቶ ተረፈ።
በደረሰበት ጉዳትም ሁለቱ ከንፈሮቹን ኣንድ ጆሮውን እና ኣንድ ጣቱን ኣጣ ፊቱም ክፉኛ ተበላሸ።
ይህ ጉዳይ ከደረሰበት ሁለት ዓመት በኃላም በ8 ዓመቱ ወደ አሜሪካ ኣቅንቶ ህክምና እንድያረግ ሚያስችል የቻሪቲ ፕሮግራም ደርሶት አሜሪካ ሄደ ህክምና ተደረገለት በዛውም እሱን በጉዲፈቻ ምያሳድጉ ቤተሰቦች አገኘ።ጥሩ ህክምና ያገኘው ሲቦማናም ታድያ ለፍሪስታይል ሪስሊንግ ልዩ ፍቅር አደረበት ልምምዱንም ጠንክሮ መስራት ቀጠለ።
አሁን 18 ዓመቱ ላይ ነው።በቅርብ በተደረገ የአፍሪካ ፍሪስታይል ሬስሊንግ ውድድርም በሶስት ቀን ውስጥ ሁለት ወርቅ ሜዳልያን ለሀገሩ ኮንጎ አስገኝቷል።ሲቦማና በወጣትም ይሁን በአዋቂ ምድብ ባረጋቸው 34 ፍልምያዎች አንድም ጊዜ ሳይሸነፍ ሁሉንም በድል አጠናቋል።አሁን ቀጣዩን የፍሪስታይል ሬስሊንግ ይቆጣጠራሉ ተብለው ከሚጠበቁ ስፖርተኞች መሀል ግንባር ቀደሙም ነው።
አትሙት ያላት ነፍስ !!!
ምንጭ:- ተግባሩ ታምራት
30/04/2026
#መረጃ
ዛሬ የተመረቀው አዲሱ የአራዳ ፓርክ በውስጡ ምን ይዟል?
👉 5 ኪ.ሜ. የሚረዝም የውስጥ ለውስጥ የአስፓልት መንገድ
👉 የእግረኛ መንገድ፦ 6 ኪ.ሜ. ርዝመት ያለው ምቹ የእግር ጉዞ መስመር።
👉 የብስክሌት መስመር፦ 5 ኪ.ሜ. ርዝመት ያለው የሳይክል ሌን።
👉 የመሮጫ ትራክ፦ 5 ኪ.ሜ. የሚረዝም ለስፖርተኞች የተዘጋጀ መስመር።
👉 የንግድ ሱቆች፦ ከፒያሳ ለተነሱ ነጋዴዎች ቅድሚያ የተሰጠባቸው 131 ዘመናዊ ሱቆች።
👉 ምግብና መጠጥ፦ 7 ካፌዎችና ሬስቶራንቶች።
👉 ዘመናዊ የስፖርት አሬና፦ አንድ (1) ዘመናዊ የአካል ብቃት ማዕከል (Gym) እና 7 አዳራሾች።
👉 መድረኮች፦ 8 ፕላዛዎችና 3 አንፊ-ቴአትሮች (ለተለያዩ ኩነቶች ማዘጋጃ የሚውሉ)።
👉ልዩ ውበት፦ በአይነቱ ልዩ የሆነ “ዳንሲንግ ፋውንቴን” (ተንቀሳቃሽ ፏፏቴ)።
👉 ብሔራዊ ምልክት፦ በሀገራችን ረጅሙ የሆነው ባለ 100 ሜትር የብሔራዊ ሰንደቅ ዓላማ መስቀያ።
👉የሕፃናት መጫወቻ፦ 4 በሚገባ የተሟሉ ዘመናዊ የመጫወቻ ስፍራዎች።
👉 አረንጓዴ ልማት፦ 15 ሄክታር መሬት በሳርና በተክሎች የተሸፈነ፣ በፓርኩ ውስጥ በተለያዩ ቦታዎች የሚገኙ 22 የሕዝብ መጸዳጃ ቤቶች።
👉 ፓርኪንግ፦ በአንድ ጊዜ 280 መኪናዎችን መያዝ የሚችል ሰፊ ማቆሚያ ወዘተ አገልግሎቶችን አካትቷል።
fans
25/04/2026
ኬኔዲ መንገሻና ብርቱካን ዱባለ
•በይ ላኪልኝ ጃኖ በይ ላኪልኝ ኩታ
አሰሪልኝ ጃኖ ፈተይልኝ ኩታ
ሲበርደኝ እንድለብሰው ማታ
•ልላክልህ ጃኖ ልላክልህ ኩታ
ላሰራልህ ጃኖ ልፍተልልህ ኩታ
ትዝ እንድልህ ትዝ እንድልህ የጥንቱ ትዝታ
•ልላክልሽ በቅሎ ልላክልሽ ፈረስ
ልላክልሽ በቅሎ ልሌክልሽ ፈረስ
የኔ አለም የልብሽ እንድደርስ
•ወይ ላክልኝ ፈረስ ወይ ላክልኝ ፈረስ
ወይ ላክልኝ በቅሎ ወይ ላክልኝ ፈረስ
ስትናፍቀኝ ስትናፍቀኝ ሌት ገስግሼ እንድደርስ
•ትቼያታለሁ ብለህ አውርተሃል አሉ
አይሰማ መስሎህ ያወራከው ሁሉ
ብወድህ ምናለ ባፈቅርህ ምናለ
ሰው ወዶ መሳሳት ዛሬ አዲስ አይደለም
… ዛሬ አዲስ አይደለም
•ተይ ጋምዬ… እንድህ አለ ብሎ
ተው ጋምዬ… ማነው የነገረሽ
ተው ጋምዬ… ድሮም ምቀኛ ሰው
ተው ጋምዬ… ምን ያወራል ብለሽ
ተው ጋምዬ…ምን ያወራል ብለሽ
ተው ጋምዬ…እንኳንስ ልተውሽ
ተው ጋምዬ…ጨክኜ ልጥልሽ
ተው ጋምዬ…በምኑም በምኑም
ተው ጋምዬ…ከአፌም አልነጥልሽ
•ያም መጥቶ እንዲህ ነው ሲሉኝ
ያም መጥቶ ትቶሻል ሲለኝ
በነገር ሆዴን ሲያቆሰለኝ
ኧረ እንዴት እውነት አይመስለኝም
•የኔ ሸጋ የኔ ሸጋ እንዴት አይመስለኝም
•እመኚኝ አንቺው በርትተሽ
ጠብቂኝ ይልቅ በርትተሽ
ወሬኛውን ትተሽ
•ኧረ እንዴት ልመንህ እኔ
ኧረ እንዴት ልመንህ እኔ
አጥቼህ ከጎኔ…
…ይቀጥላል
12/04/2026
መረጃ ፦ ዩናይትድ ኪንግደም በሆርሙዝ ሰርጥ ላይ በሚደረገው የአሜሪካ የባህር ላይ ከበባ እንደማትሳተፍ አስታወቀች።
ትራምፕ ቀደም ብሎ በሰጠው መግለጫ “ዩናይትድ ኪንግደም የጦር መርከቦችን በመላክ ታግዛለች፣ ምናልባትም ሌሎች አገሮችም እንዲሁ ያደርጋሉ” ሲል ተናግሮ ነበር።
09/04/2026
🏗️⚡🇪🇹 Ethiopia Electric Utility Headquarters – Rising Above Addis Ababa
📍 Location: Mexico Square, Addis Ababa
🏢 Structure: 5B + G + 2M + 63 Floors + 7 Upper Floors
📏 Height: 327.5 meters (300m+ landmark)
💰 Estimated Cost: 7 Billion Birr
📐 Plot Size: 20,792 m²
🏗️ Total Floor Area: 208,724 m² (subject to change)
የኢትዮጵያ የኤሌክትሪክ ኃይል ዋና መሥሪያ ቤት በአሁኑ ጊዜ በሜክሲኮ አደባባይ እየተገነባ ያለ ግዙፍ 63 ፎቅ ሰማይ ጠቀስ ሕንፃ ነው። ለኢትዮጵያ የኤሌክትሪክ ኃይል (EEP) ማዕከላዊ የአስተዳደር ማዕከል ሆኖ እንዲያገለግል የተነደፈው ይህ ታዋቂ ግንብ የአገሪቱን የኤሌክትሪክ ኃይል ማመንጨት፣ ማስተላለፍ እና ስርጭት በማስተዳደር ረገድ ወሳኝ ሚና ይጫወታል።
🌍 ግንባታው ሲጠናቀቅ፣ ከሰሃራ በታች ባሉ የአፍሪካ ክፍሎች ካሉት ረጃጅም ሕንፃዎች አንዱ ለመሆን ተዘጋጅቷል፤ ይህም የአዲስ አበባን ሰማይ ጠቀስ ሕንፃ እንደገና የሚገልጽ እና እያደገ የመጣውን የኢትዮጵያን መሠረተ ልማትና ምኞት የሚያመለክት ነው።
08/04/2026
የኢራናውያን (ፋርሳውያን) የዘር መነሻ
ኢትዮጵያ እንደሆነ ያውቁ ይሆን?
ብዙዎቻችን ስለ ፋርስ (Persia) ስልጣኔ ስናስብ ከአፍሪካ እጅግ የራቀና የተለየ ታሪክ ያለው ይመስለናል፡፡ ነገር ግን ነገሩ እንዲህ አይደለም!
ታዋቂው የታሪክ ምሁር ፕሮፌሰር ሮይ ካሳግራንዳ
(Roy Casagranda) ጥንታውያን የግሪክ ድርሳናትን ዋቢ
በማድረግ እጅግ አስገራሚ እውነትን ይፋ ያደርጋል፡፡
ለመሆኑ የዛሬዋ ኢራን ስሟንና የንግሥና መሠረቷን ያገኘችው ከኢትዮጵያዊቷ ልዕልት አንድሮሜዳ ማኅፀን እንደሆነ ያውቃሉ?
እስኪ ታሪኩን በጥቂቱ ላጫውታችሁ...
የፋርስ እናት ፧ ኢትዮጵያዊቷ አንድሮሜዳ
ታሪኩ የሚጀምረው እዚሁ ጥንቷ ኢትዮጵያ ውስጥ ነው፡፡
የኢትዮጵያ ንጉሥ ሴፊዎስ (Cepheus) እና ንግሥት ካሲዮፒያ(Cassiopeia) አንድሮሜዳ የምትባል እጅግ ውብ ልጅ ነበሯቸው፡፡
በግሪክ አፈ-ታሪክ መሠረት፡ ጀግናው ፐርሲየስ
አንድሮሜዳን ከሞት ካዳናት በኋላ ጋብቻ መሠረቱ፡፡
እነዚህ ጥንዶች በኢትዮጵያ ምድር ሳሉ "ፐርሰስ" (Perses)
የተባለ የበኩር ልጅ ወለዱ፡፡ ፕሮፌሰር ሮይ ካሳግራንዳ
እንደሚያብራራው፣ ይህ ልጅ በአያቱ በሴፊዎስ ቤተ-መንግሥት አድጎ የኢትዮጵያን ዙፋን ወረሰ፡፡ ቆይቶ ግን ወደ ምሥራቅ በመጓዝ አሁን ፋርስ (Persia) የምንለውን ግዛት መሠረተ፡፡
"ፐርሺያ" የሚለው ስያሜ የመጣውም ከዚሁ ከኢትዮጵያዊቷ አንድሮሜዳ ልጅ ከፐርሰስ ስም እንደሆነ የታሪክ አባት የሚባለው ሄሮዶተስ በድርሳናቱ አረጋግጧል!
"ሁለቱ ኢትዮጵያዎች" ፧ የሄሮዶተስ ምስክርነት
ሮይ ካሳግራንዳ በጥንቱ የግሪክ እይታ "ኢትዮጵያ" የሚለው ስም ትርጕሙ "ፊቱ በፀሐይ የተቃጠለ ሕዝብ" ማለት እንደሆነ ይነግረናል፡፡
ሄሮዶተስም ዓለምን ለሁለት ከፍሎ "ምሥራቃዊ"
እና "ምዕራባዊ" ኢትዮጵያውያን ይላቸው ነበር፡፡
ምዕራባዊያኑ∶ እኛ አፍሪካውያኑ (የዓባይ ሸለቆ ሕዝቦች)
ስንሆን፣ ምሥራቃዊያኑ ደግሞ የዛሬዎቹ ኢራናውያን (ፋርሳውያን) ናቸው፡፡
እንደ ፕሮፌሰሩ ትንታኔ፣ እነዚህ ሁለት ሕዝቦች በታሪክም ሆነ በዘር እጅግ የተሳሰሩና በጥንቱ ዓለም በአንድ "ኢትዮጵያዊነት" ጥላ ሥር የሚታዩ ነበሩ፡፡
በአጠቃላይ ኢትዮጵያዊነት ከአንድ አህጉር ያለፈ፣ የጥንቱን ዓለም ሥልጣኔ የመሪ ታላቅ የዘር ሐረግ ነው፡፡
ዛሬ በፖለቲካና በጂኦግራፊ ብንራራቅም፣ የታሪክ ድርሳናት ግን ኢራናውያን የኢትዮጵያዊቷ አንድሮሜዳ የልጅ ልጆች እንደሆኑ ይመሰክራሉ!
ምንጭ፦ የታሪክ ፕሮፌሰር ሮይ ካሳግራን (Roy Casagranda)
እንግዲህ ወደ ኋላ ሄደህ መጠየቅ ነው እንደውም ኢራን ከወሎ ነች 🤷🏽♂️