Maba Tech info

Maba Tech info

Share

heaven citizens deu 6:4

25/05/2026
19/05/2026

በ30 ቀን ውስጥ በቁ የአንድ ሙያ ባለቤት መሆን ይፈልጋሉ ??
✅እንግዲያስ ወሳኝ👌 ወደሆነው ተቋማችን ይምጡና ሕልሞወን እዉን ያድርጉ 🙏🙏

14/05/2025

#በሃዋሳ ሚሊኒየም አደባባይ #ከግንቦት 14_17 2017 ዓ.ም ድረስ ታላቅ #መንፈሳዊ ኮንፈረንስ ይካሄዳል

በኢትዮጵያ ሐዋርያት ቤተክርስቲያን የሀዋሳ ቅ/ሰበካ ሀገር አቀፍ ዓመታዊ ኮንፍረስ በሚሊኒየም አደባባይ ከ ግንቦት 14_17 2017 ዓ.ም በታላቅ መንፈሳዊ ድምቀት ይካሄዳል።

ሐሙስ ዕለት ግንቦት 14/2017 ከጧቱ 5 ሰዓት ጀምሮ አርብ, ቅዳሜ እና እሁድ ሙሉ ቀን በምኖረን ፕሮግራም እርሰዎም ተገኝተው የበረከት ተካፋይ እንደሆነ በአክብሮት ተጋብዘዋል።

The National Annual Conference of the Hawassa Parish of the Ethiopian Apostolic Church will be held in Millennium Square from May 14-17, 2017 with great spiritual splendor.

On Thursday, May 14, 2017 starting at 5:00 am(LT), you are cordially invited to participate in our all-day program on Friday, Saturday and Sunday.

17/03/2025

በኢትዮጽያ ሐዋሪያዊት ቤተክርስቲያን ታላቅ ዓመታዊ የአለምአቀፉ ኮንፈረንስ ( ዋራ ቤቴል ) በሰላም ተጠናቀቀ።

የሰላምና መቻቻል ተምሳሌት በሆነችው ሲዳማ ክልል ላለፉት አራት ቀናት ሲካሄድ የነበረው 34ኛው የአለምአቀፉ ሐዋሪያዊት ቤተክርስቲያን ታላቅ አመታዊ ኮንፈረንስ ከአንድ ሚሊዮን በላይ ምዕመናንና ታላላቅ የሀይማኖት መሪዎችና አባቶች፣ ከተለያዩ ሀገራት፣ ከአጎራባች ዞኖችና ክልሎች አንዲሁም አከባቢዎች የተሳተፉበት በትላንትናው ዕለት በሰላም መጠናቀቁ ተገልጿል።

ቤተክርስቲያኗ የሰው ልጅ በሰብአዊነት በፈሪሃ እግዚአብሔር እንዲያድጉ ኮትኩተው ከማሳደግ ጀምሮ ወደ ዘላለማዊ መንገድ እንዲጓዙ ከማደረጉ ባሻገር በሰብአዊ ድጋፍ አቅም ሌላቸው ወገኖች የምትደግፍ ሲሆን በዚሁ በዘንድሮ ኮንፈረንስም በሲዳማ ክልል ዳሌ ወረዳ ዋራ ሜዳ አከባቢው ማህበረሰብ የጤና አገልግሎት የሚውል ጤና ጣቢያ በቤተክርስቲያኗ ተሰርቶ አገልግሎት ለመስጠት መዘጋጀቱም ታዉቋል።

በኢትዮጵያ ሐዋሪያዊት ቤተክርስቲያን ያካሄደው 34ኛው ዋራ ቤቴል ጉባኤ ከመጋቢት 4 እስከ 7/2017 ዓ.ም በነበረው ኮንፈረንስ ምዕመናኑ ለሀገራችን ሰላምና መረጋጋት ለፈጣሪያቸው ፀሎትና ምልጃ ያደረሱ ስሆን በፕሮግራሙ የኢትዮጵያ ሐዋሪያዊት ቤተክርስቲያን ዋና አስተዳዳሪ ቢሾፕ ደጉ ከበደ፣ ቢሾፖች፣ ቄሶች፣ የቀድሞ የኢትዮጵያ ጠቅላይ ሚኒስቴር ቄስ ኃይሌማርያም ጨምረው ከአንድ ሚሊዮን በላይ ምዕመናን ተካፍለዋል።

በተካሄደው በዚሁ አመታዊ ኮንፈረንስ ከዓለም ዙሪያ ሁሉ ለእርሱ የተመረጡት መጥተው በዋራ ሜዳ ላይ የሰማዩን ንጉሥ ኢየሱስ ክርስቶስን በሃሌሉያና በእልልታ ደምፅ ከፍ ያደረጉ ሲሆን 👉5306👈አዲስ ነፍሳት በኢየሱስ ክርስቶስ ስም ለኃጥአታቸው ስርየት ተጠምቀው ወደ ቤተክርስቲያኗ መቀላቀላቸውን ያገኘነው መረጃ ያመለክታል።

ዋራ ቤቴል ከሰሜን፣ ከደቡብ፣ ከምስራቅና ከምዕራብ ከተለያዩ አለም ሀገራት ያለዘር፣ ቋንቋና ነገድ ልዩነት በአንድ ልብና ፍቅር የተሰበሰቡ በደሙ የተዋጁ የጌታ የኢየሱስ ክርስቶስ ልጆች በዚህ ዓለም ብቻ ሳይሆን ሊመጣ ባለው ዓለም ደግሞ ከሚጠራበት ስም ሁሉ በላይ የሆነውን የታላቁን አምላክ የኢየሱስ ክርስቶስን ስም እየጠሩ በፊቱ ሲሰግዱና ሲዘምሩ፣ በደዌና በአጋንንት የታሰሩ ሲፈቱ፣ ያየንበት፣ ከዚህ ጨለማ ዓለም አንዱን አምላክ ከምያስክድ ክፉ ትምህርት ሰዎች በንስሐ ሲመለሱ የታየበት ሚሊዮኖች በጉጉት የሚጠብቁት ጉባኤ" እንደሆነ ይነገራል።

በኢትዮጽያ #ሐዋሪያዊት ቤተክርስቲያን🙏

30/11/2024

በቤተክርስቲያናችን ለወንጌልና ለዶክትሪን የምንተጋውን ያህል ለመንፈስ አንድነት እንተጋለን። ቢሾፕ ደጉ ከበደ (በ55ኛ ዓ.ም በአገልጋዮች ሴሚናር ላይ የተናገሩት)

የእውነተኛዋ ቤተክርስቲያን የጅማረዋ እሳት የተለኮሰው ከኢየሩሳሌም ነው የፍጻሜዋ ለንጥቀት የሚያዘጋጅ እሳት የሚወጣው ግን ከኢትዮጵያ ነው ይህም ዓለምን ያጥለቀልቃል። (ቢሾፕ አማዶር)

“ወደዚያም ኮረብታ በደረሰ ጊዜ፥ እነሆ፥ የነቢያት ጉባኤ አገኙት፤ የእግዚአብሔርም መንፈስ በኃይል ወረደበት፥ በመካከላቸውም ትንቢት ተናገረ።” (1ኛ ሳሙ 10፥10)

ዓመታዊ የአገልጋዮች ሴሚናር በዋራ ሜዳ ሳስብ ከግብፅ የወጣውን የእስራኤልን ልጆች ከነዓንን አንግበው እየተጓዙ ሳሉ ድፍን አንድ ዓመት በሲና ተራራ እግዚአብሔር አስተምሯቸዋል፤ ለቀጣዩ የአሕዛብን አገራት የሚወርሱበትን መንፈሳዊ ትጥቅና አደራረግ መክሯቸዋል ሕግና ስርዓት ጽፎ ሰጥቷቸዋል፤ ደግሞ ደጋግሞ አሳስቧቸዋል፤ በታሪክ ለመጀመሪያ ጊዜ ለእግዚአብሔር ሥራ ብቻ የሚለዩ አገልጋይ ካህናት እንዲሆን አንድን ነገድ ለራሱ ሥራ ብቻ ለይቷል ይህም የሌዊ ልጆች ሆኗል።

እግዚአብሔር እስራኤልን ሲያስተምርም በየምድባቸው አድርጓል ይህንንም ያደረገው በሦስት ተራ ነበር።

1ኛ. ሙሴን ለብቻው (ዘጸ 19፥3 )
2ኛ. ሰባ ሽማግሌዎችን (አገልጋዮችን) (ዘኅ 11፥16) ሌዋውያኑም እንዲሁ
3ኛ. ጠቅላላውን የእስራኤል ሕዝብን (ዘኅ 8፥9)

የእስራኤል ልጆች በእነዚያ በአንድ ዓመት የሲና ተራራ ዙሪያ በቆየባቸው ጊዜአት ከአሥር ጊዜ ያላነሰ ሙሴ ወደሲና ተራራ እንደወጣና ከእግዚአብሔር ጋር ምክክር እንዳደረገ መጽሐፍ ቅዱሳችን ይናገራል። ውጤቱም “በእስራኤል ውስጥ መሪዎች ስለ መሩ፥ ሕዝቡም ነፍሳቸውን በፈቃዳቸው ስለ ሰጡ፥ እግዚአብሔርን አመስግኑ።” መሳ 5፥2 ይላልና።

ኢየሱስም በሥጋ በምድር በተመላለሰበት ዘመን ወደተራራ ይዟቸው እየወጣ ወደእርሱ አቅርቦ በጠንካራ ቃል የመከራቸው እና ዋኖች (ማቴ 17፥1) የተባሉ እንዳሉ እናነባለን። ይህ አድሎ አይባልም ይህ ጌታ ሰውን ከሰው ለይቶ ይመለከታል የሚያስብል የእግዚአብሔር ፍሕታዊነትን የሚጋፋ አይደለም ለአካሉና ለጋራ ዓላማ ጥቅቶችን አስታጥቆ መንፈሱን አፍስሶ ኃይሉን ሞልቶ ከድካሙ አበርትቶ ለብዙኃኑ እንዲተርፉ ያደርጋል።

“.....ሌዋውያኑም ደግሞ በፊታችሁ አለቆች ይሆናሉ፤ በርትታችሁም አድርጉ፥ እግዚአብሔርም መልካም ከሚያደርግ ጋር ይሁን።” 2 ዜና 19፥11 ተብሎ እንደተጻፈው ሌዋውያን በፊታቸው አለቆች እንዲሆኑ ይመርጣል።

የዓለም ኃይማኖት ጓዳው በሙሉ ግራ በተጋባበት በዚህ ዘመን አንድ ንግግር መናገር ቀርቶ አንድ የጋራ ስም ይዞ መቀጠል ባልቻሉበት የባቢሎንን የግንብ ሠራተኞችን ቋንቋቸው ያደባለቀ አምላክ እጁ ዛሬም አለችበት እላለሁ። ሰንሰለታማ የአመራር አሠራርን ተዋረድ የማይቀበሉ ሰማይ ተኮር ሳይሆን ገንዘብ ተኮር በሆነበት ዘመን ይህችን ቤተክርስቲያን ከአሜሪካ እስከ አውስትራሊያ ከደቡብ አፍርቃ እስከኢስያ በዓለም በአራቱም ማዕዘናት ተበታትነው የሐዋርያትን እውነት በመስዋዕትነት ተሸክመው እየሮጡ ያሉ ከእሳት የተነጠቁ ትንታግ (ዘካ 3፥2) አገልጋዮች የእርስበርስ መታያ ቀኑ እነሆ ደረሰ ይሄውም በዋራ ሜዳ ላይ ቁጥራቸው አይገመትም አዲስ ለመስዋዕት የሚቀቡ ብዙ ኢያሱዎች አሉ። “የሰማይን ሠራዊት መቍጠር የባሕርንም አሸዋ መስፈር እንደማይቻል፥ እንዲሁ የባሪያዬን የዳዊትን ዘርና የሚያገለግሉኝን ሌዋውያንን አበዛለሁ።” (ኤር 33፥22) የሚል ቃል ኪዳን ስላለው ገና ብዙ ለእግዚአብሔር ሥራ ማቃቸውን ጨርቃቸውን ጥለው የሚለዩ አሉ።

ምን እንደሚል ባላውቅም እድገቷ አስፈሪ ነው፤

02/05/2024

የሚመስል ነገር

ፍቅር በሚመስል ዘረኝነት።
አንድነት በሚመስል አድመኝነት።
ሰላም በሚመስል መረጋጋት።
ደስታ በሚመስል ሣቅ።
የዋህነት በሚመስል ጅልነት።
ብልሃት በሚመስል ብልጠት።
ሴት መውደድ በሚመስል አመንዝራነት።
ቁጠባ በሚመስል ስስት።
ቸርነት በሚመስል መበተን።
መስጠት በሚመስል ብድር።
ምስጋና በሚመስል ስድብ።
ዲፕሎማሲ በሚመስል ውሸት።
ማዘን በሚመስል ከንፈር መምጠጥ።
እምነት በሚመስል ወገኛነት።
አክብሮት በሚመስል ማጎንበስ።
ምስጋና በሚመስል ምፀት።
ዓይናፋር በሚመስል መንጣሪነት።
ርኅራኄ በሚመስል ልፍስፍስነት።
ቆራጥነት በሚመስል ጭካኔ።
ዓላማ በሚመስል ሰው መፍጀት።
ትዕግስት በሚመስል ስንፍና።
ትጋት በሚመስል ችኰላ።
መዋደድ በሚመስል መላመድ።
ዝምታ በሚመስል ዱዳነት።
ግልጽነት በሚመሰል እብደት።
ምስጢር በሚመስል ባዶ ነገር።
እልልታ በሚመስል ኡኡታ።
ድጋፍ በሚመስል ፍርሃት።
ዘመናዊነት በሚመስል ወረት።
ሀገር ወዳድ በሚመስል ጥላቻ።
ራእይ በሚመስል ቅዠት........ነው።
ከዚህ ውስጥ እኛን ይገልጻል የምንለውን አንዱን እንውሰድና የሐሰት ከመራመድ የእውነት እንቁም።
ያኔ ሸክም ቀሎን የእውነት እንራመዳለን።

19/12/2023

#ለነፍሳችን እፎይታ የሚያስገኝ ታላቅ ግብዣ
እንዳትቀሩ

Want your place of worship to be the top-listed Place Of Worship in Awassa?
Click here to claim your Sponsored Listing.

Telephone

Website

Address

Hayole Traffic Light
Awassa
TRAININGCENTER