Ever Light
Updates on different situations You can get what you want,if you put here.
ድምጽ የምናሰማበት ዕድል ያስፈልገናል።
አዲስ አበባ በአንቶኒዮ ጉተሬዝ ዕይታ
14/05/2026
ኢትዮጵያ እና ፈረንሳይ በርካታ ዋና ዋና የትብብር ስምምነቶችን ተፈራርመዋል፤ ከእነዚህም ውስጥ የአገሪቱን የታዳሽ፣ የተቀናጀ፣ ዘላቂ የኃይል እና የዲጂታል ፕሮግራም ለመደገፍ የሚያስችል 54.6 ሚሊዮን ዩሮ የብድር አቅርቦት ይገኙበታል።
ሁለቱ አገራት ለ150 ሜጋ ዋት የጂኦተርማል የህዝብ-የግል ሽርክና (PPP) ፕሮጀክት አዲስ ማዕቀፍ እና የመንገድ ካርታ ተቀብለዋል። ይህ ስምምነት የንፁህ የኃይል ልማትን ለማፋጠን እና በኢትዮጵያ የኢነርጂ ዘርፍ የረጅም ጊዜ የቴክኒክ እና የፋይናንስ ትብብርን ለማጠናከር ያለመ ነው።
13/05/2026
ኢትዮጵያና ፈረንሳይ ወደ ብሩህ መጻኢ ጉዞ!
ጠቅላይ ሚኒስትር ዐቢይ አሕመድ እና ፕሬዝዳንት ኢማኑኤል ማክሮን በሳይንስ ሙዚየም ያደረጉት ጉብኝት፤ ለሁለቱ ሃገራት የመጪው ዘመን የላቀ ፈጠራ፣ ቴክኖሎጂ እና ከፊታችን ላሉ ሰፊ ዕድሎች ያላቸውን የጋራ ቁርጠኝነት ያንጸባረቁበት ነው።
የጠነከረ ዲፕሎማሲያዊ ግንኙት፣ ጥብቅ ወዳጅነት።
11/05/2026
"ኢትዮጵያ አድዋ ላይ ድል ባታደርግ ኖሮ፤ዛሬ ላይ አፍሪካ የምትኮራበት ታሪክ አይኖራትም ነበር።
መላው አፍሪካ አዲስ አበባን እንደ ቤታቸው አድርገው ይመለከታሉ፤ ምክንያቱም ኢትዮጵያ የነፃነት እናት አገር ነች!!"
የኬንያ ጠበቃ፣ አክቲቪስት እና የፓን-አፍሪካኒስት ተናጋሪ ፕሮፌሰር ሎች ኦቲኖ ሉሙምባ ።
04/05/2026
የፌዴራል ቤቶች ኮርፖሬሽን በደቡብ ሱዳን ጁባ ከተማ በቤት ግንባታ ዘርፍ መሰማራት የሚያስችለውን ስምምነት ፈጸመ
******
የፌዴራል ቤቶች ኮርፖሬሽን በደቡብ ሱዳን ጁባ ከተማ በቤት ግንባታ ዘርፍ መሰማራት የሚያስችለውን ታሪካዊ ስምምነት ተፈራርሟል።
በሁለቱ አገራት መካከል በመሪዎች ደረጃ የጋራ የልማት ትብብር በሚፈልጉ ጉዳዮች ላይ አብሮ ለመስራት ስምምነት መደረሱን ተከትሎ በኮርፖሬሽኑ እና በደቡብ ሱዳን ማዕከላዊ ኢኳቶሪያል ግዛት መካከከል በቤት ልማት ላይ በጋራ ለመስራት የሚያስችል ስምምነት ተፈጽሟል፡፡
በኢትዮጵያ ፌዴራል ቤቶች ኮርፖሬሽን እና በደቡብ ሱዳን የማዕከላዊ ኢኳቶሪያል ግዛት መንግሥት መካከል የተደረገው ይህ የመግባቢያ ሰነድ፣ በጁባ ከተማ በቤቶች ልማትና አስተዳደር ዘርፎች በጋራ ለመሥራት የሚያስችል መሠረት ጥሏል።
ስምምነቱን የፌዴራል ቤቶች ኮርፖሬሽን ዋና ሥራ አስፈጻሚ ዶ/ር ረሻድ ከማል እና የማዕከላዊ ኢኳቶሪያ ግዛት መንግሥት አስተዳደሪ ሚስተር ኢማኑኤል አዲል በይፋ ፈርመዋል።
ይህ ውል ኮርፖሬሽኑ ያለውን የረጅም ጊዜ ልምድና የቴክኒክ አቅም በመጠቀም በጁባ ከተማ ዘመናዊ የመኖሪያ ቤቶች፣ የንግድ ሕንፃዎችና የመንግሥት መሥሪያ ቤቶች ግንባታ እንዲያከናውን ሰፊ መንገድ ይከፍታል።
የፌዴራል ቤቶች ኮርፖሬሽን ዋና ሥራ አስፈጻሚ ዶ/ር ረሻድ ከማል በሥነ ሥርዓቱ ላይ እንደተናገሩት፣ ኮርፖሬሽኑ ባስቀመጠው ራዕይ መሠረት በምሥራቅ አፍሪካና በመላው አህጉሪቱ ገበያዎች ለመሰማራት ከፍተኛ ዝግጅት ሲያደርግ ቆይቶ አሁን ላይ ወደ ተግባር ምዕራፍ ተሸጋግሯል።
ኮርፖሬሽኑ ስትራቴጂካዊ ጠቀሜታ ያላቸውና አዋጭ በሆኑ ፕሮጀክቶች ላይ ትኩረት አድርጎ እየሠራ መሆኑንም ዋና ሥራ አስፈጻሚው አብራርተዋል።
የማዕከላዊ ኢኳቶሪያ ግዛት መንግሥት አስተዳደሪ ሚስተር ኢማኑኤል አዲል በበኩላቸው፣ በኢትዮጵያ እየተመዘገበ ያለው ኢኮኖሚያዊ ዕድገትና ፈጣን የከተሞች ለውጥ ለመላው አፍሪካውያን ተምሳሌት እየሆነ መሆኑን ገልጸው፣ በቆይታቸውም በርካታ የልማት ሥራዎችን ተዘዋውረው መመልከታቸውን ገልጸዋል።
በተለይም በቤት ልማት ዘርፍ በኢትዮጵያ ያለውን ተሞክሮ ከኮርፖሬሽኑ ጋር በመሆን በጁባ ከተማና በግዛቱ ተግባራዊ ለማድረግ እንደሚሠሩ አስተዳደሪው አረጋግጠዋል።
ስምምነቱ በሁለቱ አገራት መካከል ያለውን የኢኮኖሚ ትስስር ከማጠናከር ባሻገር፣ ኮርፖሬሽኑ በቤት አስተዳደርና ልማት ያለውን ውጤታማ ተሞክሮ ለግዛቱ ባለሙያዎች የሚያጋራበትንና የአቅም ግንባታ ሥልጠናዎችን የሚሰጥበትን ዕድል ያመቻቻል።
የስምምነቱን አፈጻጸም በቅርበት የሚከታተል፣ ዝርዝር የፕሮጀክት ሰነዶችን የሚያዘጋጅና አጋዥ የመፍትሔ ሐሳቦችን የሚያመነጭ የጋራ ቴክኒክ ኮሚቴ እንዲቋቋምም ተወስኗል።
ይህ ስምምነት የሁለቱ አገራት የሁለትዮሽ ግንኙነት ወደ ላቀ ደረጃ ከማሸጋገሩም በላይ፣ የኢትዮጵያን የቤቶች ልማት ተሞክሮ ወደ ጎረቤት አገራት ለማስፋፋት ትልቅ መነቃቃትን የሚፈጥር ይሆናል።
01/05/2026
⚖️ ተጠያቂነት በተግባር - የዴሞክራሲ ተቋማትን የማጠናከር ጉዟችን!
መንግስት የሀገርን ሀብት ለህዝብ ጥቅም ለማዋልና ፍትሐዊ አስተዳደርን ለማስፈን "ከራሱ አመራሮች" የጀመረ ተጠያቂነትን በተግባር እያረጋገጠ ይገኛል።
🔍 በቅርቡ የተወሰዱ ዋና ዋና እርምጃዎች፦
የህግ የበላይነት ማረጋገጥ፦ በንግድ ባንክ እና በማዳበሪያ ግዢ ላይ ከፍተኛ የሀገር ሀብት ያባከኑ (ከ5.6 ቢሊዮን ብር በላይ ኪሳራ ያደረሱ) አመራሮች ላይ ክስ ተመስርቷል።
የፀረ-ሙስና ዘመቻ፦ ብሔራዊ የፀረ-ሙስና ኮሚቴ (NACC) ከ250 በላይ ጥቆማዎችን ተቀብሎ ፈጣን እርምጃ እየወሰደ ነው።
ተቋማዊ ነፃነት፦ እንደ ምርጫ ቦርድ እና የሰብአዊ መብቶች ኮሚሽን ያሉ ተቋማት በገለልተኛ አመራርና በራሳቸው በጀት እንዲመሩ ተደርጓል።
የሽግግር ፍትህ፦ ያለፉ በደሎችን በዘላቂነት ለመፍታት የሽግግር ፍትህ ፖሊሲ ተዘጋጅቶ ወደ ትግበራ ገብቷል።
🚀 የወደፊት ትኩረታችን፦
አገልግሎቶችን ዲጂታላይዝድ በማድረግ የሙስና እድሎችን ማጥበብ እና ብቃት ያለው ሲቪል ሰርቪስ መገንባት ላይ እናተኩራለን።
💬 የእርስዎ ተሳትፎ ወሳኝ ነው!
ሙስናን መከላከል የመንግስት ብቻ ሳይሆን የእያንዳንዱ ዜጋ ኃላፊነት ነው።
የሀገርን ሀብት በጋራ እንጠብቅ
01/05/2026
🇪🇹⚡️ ከነዳጅ ጥገኝነት ወደ አረንጓዴ ኢነርጂ!
ኢትዮጵያ በኤሌክትሪክ ተሽከርካሪዎች ሽግግር የአህጉራችን ፋና ወጊ ሆና ቀጥላለች። ይህ ጉዞ የት ደረሰ? ቁልፍ ስኬቶችንና የወደፊት ግቦችን ቀጥሎ ባለው መረጃ እንቃኝ።
🚫 ታሪካዊ ውሳኔ (2016)
ኢትዮጵያ በነዳጅ የሚሰሩ ተሽከርካሪዎች ወደ ሀገር ውስጥ እንዳይገቡ በመከልከል ከአፍሪካ የመጀመሪያዋ ሀገር በመሆን ታሪክ ሰርታለች። የዚህ ውሳኔ ዓላማው በውጭ ምንዛሪ የሚገዛውን የነዳጅ ወጪ ሸክም መቀነስና አካባቢን መጠበቅ ነው።
🚗 የቁጥሮች እድገት በ2017፦
100,000 የኤሌክትሪክ ተሽከርካሪዎች ወደ ስራ ገብተዋል። በአዲስ አበባ ብቻ በቀን 90,000 መንገደኞችን በንፁህ ኢነርጂ በማጓጓዝ ላይ ይገኛሉ።
በ2018፦ ቁጥሩ ወደ 140,000 ከፍ እንዲል ታቅዶ በስፋት እየተሰራበት ነው።
🏭 የ2023 ራዕይ፦
ኢትዮጵያ የራሷን የኤሌክትሪክ መኪኖች በመገጣጠም እና በመላ ሀገሪቱ ከ400 በላይ የቻርጅ ማደያዎችን በመገንባት፣ በ2023 የኤሌክትሪክ ተሽከርካሪዎችን ቁጥርን 500,000 ለማድረስ በትጋት እየሰራች ትገኛለች።
ይህ ለውጥ ለሀገር ኢኮኖሚ ካለው ፋይዳ ባሻገር ለነገው ትውልድ ንፁህ አየርና የተስተካከለ የአየር ንብረት ለማስረከብ ትልቅ እርምጃ ነው።
እናንተስ ምን ትላላችሁ? የወደፊቱ ትራንስፖርት በኤሌክትሪክ መሆኑን ይደግፋሉ? አስተያየትዎን በኮሜንት ያጋሩን! 👇