AMAS Advocates LLP
Diligence Matters
20/03/2026
ለመላው የእስልምና እምነት ተከታዮች በሙሉ እንኳን ለ1447ኛው የዒድ አልፈጥር በዓል በሰላም አደረሳችሁ!
በዓሉ የሰላም፣ የፍቅር እና የመተሳሰብ ይሁንላችሁ፡፡
ዒድ ሙባረክ!
09/01/2026
"የባሕል ፍርድ ቤቶችን ሥራ ለማስጀመር ዝግጅቱ ተጠናቅቋል" አቶ ዓለምአንተ አግደው
ባሕር ዳር: ታኅሣሥ 20/2018 ዓ.ም (አሚኮ) የአማራ ክልል ጠቅላይ ፍርድ ቤት ፕሬዝዳንት ዓለምአንተ አግደው የባሕል ፍርድ ቤቶች እውቅና መስጠትን እና ወደ ሥራ ማስገባትን አስመልክተው መግለጫ ሰጥተዋል።
በመግለጫቸውም የባሕል ፍርድ ቤቶች እውነትን በማውጣት ፍርድን ለመስጠት አይነተኛ የፍትሕ መንገዶች ናቸው ብለዋል።
ሽምግልናን መሠረት አድርገው የሚሠሩ በመኾናቸው እርቅን በማምጣት፣ የበደለን እንዲክስ በማድረግ፣ ቁርሾን በማስቀረት ዘላቂ እና ጤናማ የማኅበረሰብ ግንኙነትን ለመፍጠር አይነተኛ ሚና አላቸው ነው ያሉት።
በመንግሥት በኩልም ዜጎች ባሕላቸውን እንዲያሳድጉ እና በመረጡት የመዳኘት መብታቸው እንዲከበር ኀላፊነት ያለበት በመኾኑ ትኩረት ተሰጥቶ እየተሠራበት መኾኑን አንስተዋል።
በክልሉ ምክር ቤት የባሕል ፍርድ ቤቶችን ለማቋቋም እና ወደ ሥራ ለማስገባት የሚያስችል አዋጅ ወጥቶ ወደ ተግባር ተገብቷል ነው ያሉት። የአዋጁን አፈጻጸም የሚከታተል በክልሉ ጠቅላይ ፍርድ ቤት ሰብሳቢነት የሚመራ የአማካሪ ምክር ቤት መቋቋሙንም ጠቁመዋል።
እስከ ቀበሌ ድረስ ጥናቶችን ማድረግ፣ የእውቅና መስጫ እና የማስተግበሪያ መመሪያ ማውጣት፣ የትግበራ ፍኖተ ካርታ እና የሥልጠና ሰነዶችን ማዘጋጀት፣ የተግባቦት ስትራቴጅ መቅረጽ እና ሌሎች ሰፊ ተግባራት ሲከናወኑ መቆየታቸውንም አንስተዋል።
የክልሉ ጠቅላይ ፍርድ ቤትም አዋጁን በተሟላ ሁኔታ ለመተግበር እና የባሕል ፍርድ ቤቶችን ሥራ ለማስጀመር ዝግጅቱን ማጠናቀቁን ገልጸዋል። ታኅሣሥ 21 እና 22/2018 ዓ.ም በክልል ደረጃ የእውቅና እና የሥራ ማስጀመሪያ መርሐ ግብር እንደሚኖርም አስታውቀዋል።
መርሐ ግብሩ ከየወረዳው የተወከሉ ሽማግሌዎች፣ የሃይማኖት አባቶች፣ አዋጁን ለማሥፈጸም ኀላፊነት የተሰጣቸው ተቋማት፣ የፌዴራል እና የክልል ከፍተኛ የሥራ ኀላፊዎች በተገኙበት እንደሚከናወንም አብራርተዋል።
በክልሉ ከ4 ሺህ በላይ በኾኑ ቀበሌዎች ሥራው እንደሚጀመርም ገልጸዋል። በባሕላዊ ፍርድ ቤቶች ተግባራዊ የሚደረጉ ሽምግልናን ጨምሮ 15 የባሕላዊ ግጭት መፍቻ ሥርዓቶች መለየታቸውንም ተናግረዋል። በቀጣይም ጥናት እየተደረገ ሊጨመር እንደሚችል ጠቁመዋል።
"የባሕል ፍርድ ቤቶች የመደበኛ ፍርድ ቤቱን የሚተኩ ሳይኾኑ ጎን ለጎን የሚሠሩ የዜጎች አማራጭ የፍትሕ ሥርዓቶች ናቸው" ብለዋል። እውቅና ሲሰጣቸውም ባሕሉ እንዲዳብር ታሳቢ የተደረገ መኾኑንም ገልጸዋል። ለዚህም የሚሰጧቸው ውሳኔዎች በአስገዳጅነት ተፈጻሚ እንዲኾኑ ተደርጓል ነው ያሉት።
ሥራቸውን ሲሠሩም የማኅበረሰቡን የባሕል እሴት በጠበቀ መልኩ የሚያከናውኑ ይኾናል ብለዋል። የባሕል ፍርድ ቤት ዳኛ ኾነው የሚመረጡ ሽማግሌዎች ገለልተኛ እና ታማኝ ኾነው ሰብዓዊ መብቶችን እና ሕገ መንግሥቱን የማክበር ኀላፊነት እንዳለባቸውም አብራርተዋል።
ለባሕላዊ ፍርድ ቤቶች ውጤታማነት እና ለአዋጁ ተግባራዊነት የሚመለከታቸው አካላት ሁሉ የሚጠበቅባቸውን ኀላፊነት እንዲወጡም ጥሪ አቅርበዋል።
ዘጋቢ:- አሰፋ ልጥገበው
የአሚኮ ዲጂታል ሚዲያ ቤተሰብ ይሁኑ!
👇👇👇
https://linktr.ee/AmharaMediaCorporation
ለኅብረተሰብ ለውጥ እንተጋለን!
09/01/2026
አዲስ የዲፕፌክ ቴክኖሎጂ በዲጂታል የባንክ አገልግሎት ላይ ስጋት እየደቀነ መሆኑ ተገለጸ
የዓለም ኢኮኖሚክ ፎረም (WEF) ሰሞኑን ባወጣው ሪፖርት፣ በሰው ሰራሽ አስተውሎት የሚሰሩ የዲፕፌክ (Deepfake) ቴክኖሎጂዎች በዲጂታል ማንነት ማረጋገጫ ስርዓቶች ላይ ከባድ ስጋት እየፈጠሩ መሆኑን ገለጸ።
በፈረንጆቹ ጥር 8 ቀን 2026 ይፋ የሆነው ይኸው ሪፖርት፣ በተለይ የሰዎችን ፊት በሌላ የመተካት (Face-swapping) ቴክኖሎጂ ወንጀለኞች የባንክና የፋይናንስ ተቋማትን የደህንነት ስርዓት ለመስበር እየተጠቀሙበት መሆኑን ያመላክታል።
ወንጀለኞች የሰዎችን ፊት የሚቀይሩ መተግበሪያዎችን እና የሐሰት ምስሎችን በቀጥታ ወደ ካሜራ ሲስተም የሚልኩ ቴክኖሎጂዎችን (Camera Injection) በማቀናጀት፣ ተቋማት ደንበኞቻቸውን በአካል ሳይገኙ የሚያረጋግጡበትን (KYC) ሂደት እያታለሉ እንደሚገኙ የዓለም ኢኮኖሚክ ፎረም ሪፖርት ይፋ አድርጓል።
ይህ ድርጊት በተለይ በፋይናንስ ዘርፍ እና በክሪፕቶ ምንዛሬ ተቋማት ላይ ከፍተኛ የኢኮኖሚ እና የደህንነት አደጋ እየፈጠረ መሆኑ ተገልጿል።
ሪፖርቱ ለቀጣዩ አንድ ዓመት የሚስተዋሉ አምስት ዋና ዋና አዝማሚያዎችን የተነበየ ሲሆን፣ የሰው ሰራሽ አስተውሎት (AI) መሳሪያዎች በዝቅተኛ ዋጋ ለሁሉም መገኘታቸው የጥቃቱን ብዛት እንደሚጨምረው ተጠቁሟል።
ወንጀለኞች ከፋይናንስ ዘርፍ ባለፈ ዲጂታል መታወቂያ ወደሚጠይቁ ሌሎች የመንግስት አገልግሎቶች ትኩረታቸውን እንደሚያዞሩም በሪፖርቱ ተመልክቷል።
በተጨማሪም፣ በቴክኖሎጂው የሚሰሩ የሐሰት ምስሎች ጥራት እየጨመረ መምጣቱ ምስሎቹን ከእውነተኛው ለመለየት አስቸጋሪ እንደሚያደርጋቸው ተመራማሪዎቹ አስረድተዋል።
ምንም እንኳን የዲፕፌክ ቴክኖሎጂ እየረቀቀ ቢመጣም፣ አሁንም ድረስ በምስሎቹ ላይ የሚታዩ መጠነኛ ግድፈቶች መኖራቸውን ሪፖርቱ ጠቁሟል።
እነዚህም የብርሃን አለመመጣጠን፣ የንግግር እና የከንፈር እንቅስቃሴ አለመገጣጠም፣ እንዲሁም የምስል ጥራት መጓደል መሆናቸው ተገልጿል።
እነዚህን ድክመቶች በመጠቀምም የላቁ የመለያ ዘዴዎችን (Detection models) ማዘጋጀት እንደሚገባ ተመልክቷል።
የዓለም ኢኮኖሚክ ፎረም የፋይናንስ ተቋማት፣ የቴክኖሎጂ አበልጻጊዎች እና መንግስታት በጋራ በመሆን የተቀናጀ የመከላከያ ስርዓት እንዲገነቡ ጥሪ አቅርቧል።
ተጨማሪ የሳይበር ደህንነት መረጃዎችን ለማግኘት፡-
• ድረ ገጽ፦ https://www.insa.gov.et
• ፌስቡክ፡- https://web.facebook.com/INSA.ETHIOPIA
• ቲክቶክ፡- https://www.tiktok.com/?_t=8qBKkyp092r&_r=1
• ዩትዩብ፦ https://www.youtube.com//featured
• ቴሌግራም፦ https://t.me/insagovet
• ትዊተር (X) ፦ https://twitter.com/INSAEthio
• ሊንክድኢን:- https://www.linkedin.com/.../information-network.../
• የሳይበር ጥቃት ጥቆማ ለመስጠት፡- ነጻ የስልክ መስመር 933
09/01/2026
የባሕል ፍርድ ቤቶች የዳኝነት ስልጣን
ባህርዳር፣ ታህሳስ 27/2018(አብክመ ጠ/ፍ/ቤት)
የባህል ፍርድ ቤቶችን ለማቋቋም እና እውቅና ለመስጠት በወጣው አዋጅ ቁጥር 298/2017 መሰረት እውቅና ተሰጧቸው ወደ ስራ እንዲገቡ የሚደረጉ የባሕል ፍርድ ቤቶች በሚከተሉት ጉዳዮች ላይ የዳኝነት ሥልጣን ይኖራቸዋል።
የሥረ ነገር ሥልጣን
የባሕል ፍርድ ቤቶች ክርክሮችን ማየት የሚችሉት ተከራካሪ ወገኖች ጉዳያቸው በባሕላዊ ፍርድ ቤት እንዲታይ ፍቃድ ከሰጡ በኃላ ሲሆን በሚከተሉት ጉዳዮች ላይ የዳኝነት የሥረ ነገር ሥልጣን አላቸው👇
👉 የፍትሐብሔር ጉዳዮች (በገንዘብ መጠን፣ በንብረቱ እና በጉዳዩ አይነት ገደብ ሳይደረግበት)፤
👉 በግል አቤቱታ አቅራቢነት የሚታዩ የወንጀል ጉዳዮችን (አነስተኛ የወንጀል አይነቶች) እና የደንብ መተላለፍ ድርጊቶች፤
👉 በሌሎች በዐቃቢ ሕግ ክስ አቅራቢነት በሚታዩ የወንጀል ጉዳዮች ላይ የወንጀል ጉዳዩን የማየት ሥልጣን ባይኖራቸውም👇
👉 በክርክሩ ውስጥ ያሉ ወገኖችን ማስታረቅ
👉 ካሳ መወሰን እና ማስፈጸም
👉 ወጪ እና ኪሳራ የማስከፈል ሥልጣን ተሰጥቷቸዋል፡፡
👉 ከዚህ ህግ ውጪ በሌሎች ህጎች በግልጽ ተለይቶ የመወሰን ስልጣን በተሰጣቸው ጉዳዮች ላይ የዳኝነት ሥልጣን አላቸው፡፡
የግዛት ወይም አካባቢያዊ ሥልጣን
ከላይ የተመለከተው የባሕል ፍርድ ቤቶች የስረ ነገር ሥልጣን እንደተጠበቀ ሆኖ፣ የባሕል ፍርድ ቤቶች የቀረበላቸውን ጉዳይ ለማየት ከስር ከተመለከቱት መስፈርቶች መካከል ቢያንስ አንዱ የተሟላ መሆን ይጠበቅበታል 👇
👉 ከተከራካሪ ወገኖች መካከል ቢያንስ አንዱ የባሕል ፍርድ ቤቱ የሥልጣን ወሰን ስር በሚገኝ ቀበሌ ውስጥ ነዋሪ ወይም ተወላጅ ከሆነ፤
👉 ለክርክር ምክንያት የሆነው ቋሚ ንብረት የባሕል ፍርድ ቤቱ የሥልጣን ወሰን ስር በሚገኝ ቀበሌ ውስጥ የሚገኝ ከሆነ፤
👉 ለክርክር መነሻ የሆነው ጉዳይ የተጀመረው ወይም ፍፃሜ ያገኘው የባሕል ፍርድ ቤቱ የሥልጣን ወሰን ውስጥ ከሆነ ነው፡፡
👉 ከላይ አካባቢያዊ የዳኝነት ሥልጣን በሚመለከት ከተቀመጡ ማሳያዎች በተለየ መልኩ የሚያስቀምጥ የባህል ህግ በሚኖርበት ጊዜ የባሕል ሕጉ ተፈፃሚነት የሚኖረው ይሆናል፡፡
ሌሎች አዳዲስ መረጃዎችን ለማግኘት በሚከተሉት የማህበራዊ ትስስር ገጾቻችን ይወዳጁን👇
Facebook:
https://web.facebook.com/Amharascourt
Telegram:
https://t.me/Spc2016
Twitter(X):
https://x.com/Amharascourt
LinkedIn:
https://www.linkedin.com/company/amharascourt/
Tiktok:
https://tiktok.com/
You Tube :
https://www.youtube.com/
Website:
https://amhsc.gov.et
08/01/2026
በገቢ ግብር የማሻሻያ አዋጅ ቁጥር 1395/2017 ማሻሻያ የተደረገባቸው ጉዳዮች
መግቢያ
ግብር የአንድ አገር ኢኮኖሚያዊ ሉዓላዊነት ከሚረጋገጥባቸው መንገዶች አንዱ ሲሆን መንግሥትም የዜጎችን ኢኮኖሚያዊ፣ ማኅበራዊ እና ፖለቲካዊ እድገት በማረጋገጥ ረገድ ያለበትን ኃላፊነት ለመወጣት የሚያስፈልገውን ገቢ የሚያገኝበት ምንጭ ነው። የግብር ሕግ እንደማንኛውም ሌሎች ሕጎች ሁሉ ማኅበረሰቡ የደረሰበትን ሁለንተናዊ የእድገት ደረጃ ከግምት ባስገባ መልኩ ተቀርፆ በሥራ ላይ የሚውል እንደመሆኑ በየወቅቱ የሚኖሩ ማኅበራዊ፣ ፖለቲካዊ፣ ኢኮኖሚያዊ እና ሌሎች ለውጦችን ታሳቢ ባደረገ መልኩ መሻሻል ይኖርበታል።
የአገራችንም የግብር ሥርአት በየጊዜው የሚከሰቱ ለውጦችን ከግምት ባስገባ መልኩ የተለያዩ ማሻሻያዎችን በማድረግ አሁን ካለበት ደረጃ ደርሷል። በቅርቡ ማሻሻያ ከተደረገባቸው የግብር ሕግ አይነቶች አንዱ የገቢ ግብር አዋጅ ቁጥር 979/2008 ሲሆን በአዋጅ ቁጥር1395/2017 ማሻሻያ ተደርጎበታል። በዚህ አጭር ጽሑፍ የማሻሻያ አዋጁ ያካተታቸውን ዋና ዋና ጉዳዮች በአጭሩ እንዳስሳለን።
የማሻሻያ አዋጁ ያካተታቸው አዳዲስ ጉዳዮች
ከመቀጠር፣ ከቤት ኪራይ፣ ከንግድ ሥራ እና ከዕድል ሙከራ የሚገኝ የገቢ ግብር
ከመቀጠር፣ ከኪራይ፣ ከንግድ ሥራ እና ከዕድል ሙከራ የሚገኝ የገቢ ግብር ምጣኔዎች በማሻሻያ አዋጁ ማሻሻያ ተደርጎባቸዋል፡፡ ይኸውም በቀድሞ የገቢ ግብር አዋጅ (አዋጅ ቁጥር 979/2008 አንቀፅ 11) ተደንግጎ የነበረው ከግብር ነፃ ከሚሆነው ከመቀጠር የሚገኝ ወርሃዊ ገቢ መጠን ጀምሮ እስከ ከፍተኛው የግብር ምጣኔ ድረስ ማሻሻያ ተደርጎበታል፡፡ በቀድሞው ሕግ ከገቢ ግብር ነፃ የሆነው እስከ ብር ስድስት መቶ (600) ያለ ገቢ የነበረ ሲሆን በማሻሻያ አዋጁ አንቀፅ 2(6) መሠረት እስከ ብር ሁለት ሺ (2,000) ድረስ ያለ ከመቀጠር የሚገኝ ወርሀዊ ገቢ ከግብር ነፃ እንዲሆን ተደርጓል። በተጨማሪም ከፍተኛው የማስከፈያ ምጣኔ የሆነው 35% ከአስር ሺ ዘጠኝ መቶ (10,900) ብር ወርሃዊ ገቢ ጀምሮ ይጣል የነበረ ሲሆን በማሻሻያ አዋጁ ግን ይሄው የ35% ምጣኔ ከአስራ አራት ሺ (14,000) ብር በላይ ወርሀዊ ገቢ ባላቸው ተቀጣሪዎች ላይ ብቻ የሚጣል ይሆናል።
ሌላው በአዋጅ ቁጥር 1395/2017 ማሻሻያ የተደረገው በኪራይ እና ንግድ ሥራ ገቢዎች ምጣኔ ላይ ነው። በቀድሞው የገቢ ግብር አዋጅ (አንቀፅ 14(2)) እና 19(2) መሠረት እስከ ብር ሰባት ሺ ሁለት መቶ (7,200) ድረስ ያሉ አመታዊ የኪራይ እና የንግድ ሥራ ገቢዎች ከግብር ነፃ የነበሩ ሲሆን ይኸው መጠን በማሻሻያ አዋጁ አንቀፅ 2(😎 እና 2(10) መሠረት ማስተካከያ ተደርጎበት ወደ ብር ሃያ አራት ሺ (24,000) አመታዊ የኪራይ እና የንግድ ሥራ ገቢ ከፍ እንዲል ተደርጓል። ከፍተኛው የ35% የግብር ምጣኔ የሚጣልበትን የኪራይ እና የንግድ ሥራ የገቢ መጠን በተመለከተ በማሻሻያ አዋጁ በቀድሞ አዋጅ ከነበረው ከብር አንድ መቶ ሰላሳ ሺ ስምንት መቶ (130,800) በላይ ከፍ በማድረግ ከብር አንድ መቶ ስልሳ ስምንት ሺ (168,000) በላይ አመታዊ ገቢ ላይ እንዲሆን ተደርጓል።
ሌላኛው ከግብር ምጣኔ አንፃር ለውጥ የተደረገው ከዕድል ሙከራ በሚገኙ ገቢዎች ላይ ነው። ቀደም ሲል ከዕድል ሙከራዎች ገቢ ያገኘ ሰው የገቢውን 15% (አስራ አምስት በመቶ) ግብር እንዲከፍል የሚደረግ ሲሆን (አዋጅ ቁጥር 979/2008 አንቀፅ 57(1)፤ በማሻሻያ አዋጁ አንቀጽ 2(22) መሰረት ከዕድል ጨዋታ ገቢ ያገኘ ሰው ከገቢው ላይ 20% (ሃያ በመቶ) ግብር መክፈል ይጠበቅበታል። ነገር ግን ይሄ የግብር መጠን በዕድል ሙከራ ከአንድ ሺ ብር በታች ባገኘ ሰው ላይ አይጣልም።
የግብር ከፋይ ደረጃዎች
ሌላኛው በማሻሻያ አዋጁ ለውጥ ከተደረገባቸው ነጥቦች መካከል አንዱ የግብር ከፋይ ደረጃዎችን የተመለከተው ነው። በቀድሞው የገቢ ግብር አዋጅ 979/2008 አንቀፅ 3 መሠረት የደረጃ “ሀ”፣ “ለ” እና “ሐ” በሚል በሶስት የግብር ከፋይ ደረጃዎች ከፋፍሎ ያስቀመጣቸው ሲሆን ክፍፍሉም ጠቅላላ አመታዊ ገቢን ታሳቢ ያረገ ነው። በዚህም መሰረት ድርጅት ወይም ጠቅላላ አመታዊ ገቢው ብር አንድ ሚሊዮን (1,000,000) ወይም ከዚያ በላይ የሆነ ማንኛውም ሰው በደረጃ “ሀ” ስር የሚመደብ ሲሆን፣ ከብር አንድ ሚሊዮን (1,000,000) በታች እና ከብር አምስት መቶ ሺ (500,000) በላይ አመታዊ ገቢ ያላቸው (ድርጅቶችን ሳይጨምር) ደግሞ ደረጃ “ለ” ስር ይጠቃለላሉ። ድርጅትን ሳይጨምር አመታዊ ጠቅላላ ገቢው ከብር አምስት መቶ ሺ (500,000) በታች የሆኑ ግብር ከፋዮች በደረጃ “ሐ” ስር ይመደባሉ።
ነገር ግን በማሻሻያ አዋጁ አንቀፅ 2(2) መሠረት በሶስት ደረጃዎች የመክፈሉ ሂደት ቀርቶ የግብር ከፋዮች ደረጃ “ሀ” እና “ለ” በሚሉ ሁለት ደረጃዎች ብቻ እንዲከፈል ተደርጓል። ከአመታዊ ገቢ ምጣኔውም አንፃር ቀደም ሲል የነበረው እንዲሻሻል ተደርጎ በደረጃ “ሀ” ስር የሚወድቁ ግብር ከፋዮች ድርጅቶች ወይም ጠቅላላ አመታዊ ገቢያቸው ከብር ሁለት ሚሊዮን (2,000,000) እና በላይ የሆኑ ሌሎች ሰዎች ሲሆኑ ከዚህ መጠን በታች የሆነ ጠቅላላ አመታዊ ገቢ ያላቸው ሰዎች (ድርጅቶችን ሳይጨምር) በደረጃ “ለ” ስር እንዲመደቡ ተደርጓል።
የገቢ ምንጭ (የታክስ መሰረት) ማስፋት
የገቢ ግብር ማሻሻያ አዋጁ በቀድሞው አዋጅ ያልነበረ አዲስ የግብር ምንጭ አካቶ የወጣ ነው። ይኸውም በማሻሻያ አዋጁ ላይ ከዲጂታል ይዘት ፈጠራ የሚገኝ ገቢም ግብር እንደሚከፈልበት በግልፅ ተደንግጓል። በገቢ ግብር የማሻሻያ አዋጅ አንቀፅ 2(1) መሰረት ከዲጂታል ይዘት ፈጠራ የሚገኝ ገቢ ማለት አንድ ግለሰብ ወይም ድርጅት የቪዲዮ ማጋሪያ አገልግልቶችን፣ የማኅበራዊ ሚዲያ መድረኮችን፣ የድምጽ ማስተላለፊያ (ፖድካስት) አገልግሎቶችን እና የቀጥታ ስርጭት መድረኮችን ጨምሮ በኦንላይን (በበይነ መረብ) መድረኮች ላይ ዲጂታል ይዘትን በመፍጠር እና በማሰራጨት የሚያገኘው ማንኛውም በገንዘብ ወይም በአይነት የሚገኝ ገቢ ነው። ይህም ከማስታወቂያዎች እና ስፖንሰርሺፖች፣ ከምርት ስም ስምምነቶች እና ድጋፎች፣ ከአጋርነት ግብይት እና የምርት ምደባዎች፣ ከደጋፊዎች አስተዋጽኦ፣ ከገንዘብ ስጦታዎች ወይም የብዙሃን የገንዘብ ማሰባሰብ (ክራውድ ፈንዲንግ)፣ ከአባልነት ክፍያዎች፣ ከዲጂታል ወይም ከአካላዊ ሸቀጦች ሽያጭ፣ ከማስተዋወቂያ እንቅስቃሴ ምትክ የተገኙ ዕቃዎች ወይም አገልግልቶች እና ተመሳሳይነት ያላቸው ሌሎች ክፍያዎችን ያካትታል፡፡ በዚህም መሠረት በኢትዮጵያ ነዋሪ ወይም ነዋሪ ያልሆነ ሰው በኢትዮጵያ ውስጥ የዲጂታል አገልግሎት በመስጠት ከሚያገኘው ገቢ 5% የማይበልጥ የገቢ ግብር እንደሚከፍል በአዋጅ አንቀጽ 2(17 ተደንግጓል)። የዲጂታል አገልግሎት ምንነትን በተመለከተ፣ የማስከፈያ ምጣኔ፣ የአከፋፈል ሁኔታ እና ሌሎች ተያያዥነት ዝርዝር ጉዳዮችን በተመለከተ የሚንስትሮች ምክር ቤት በሚያወጣው ደንብ መሠረት የሚወሰን ስለመሆኑ በማሻሻያ አዋጁ ተጠቅሷል።
ከዲጂታል ይዘት ፈጠራ ሥራው ትርፍ ለማግኘት ታስቦ በመደበኛነት የሚከናወን ከሆነ፣ ፈጣሪው ድርጅት ከሆነ፣ የሂሳብ መዝገብ የሚያዝ ከሆነ ወይም ከንግድ ጋር የተያያዙ ወጪዎች ተቀናሽ የሚደረጉለት ከሆነ የሚገኘው ገቢ እንደ ንግድ ሥራ ገቢ እንደሚቆጠር ከማሻሻያ አዋጁ አንቀጽ 2(11) መረዳ ይቻላል፡፡ ከእነዚህ ሁኔታዎች ውጭ ከዲጂታል ይዘት ፈጠራ የሚገኙ ገቢዎች እንደሌላ ገቢ ተቆጥረው በአዋጁ ሠንጠረዥ “መ” መሠረት ግብር የሚጣልባው ሲሆን ዝርዝር አፈፃፀሙም በሚኒስትሮች ምክር ቤት በሚወጣ ደንብ መሠረት የሚወሰን ይሆናል። ስለሆነም የዲጂታል ይዘት አመንጪዎች እንደማንኛውም ግብር ከፋይ ሁሉ መለያ ቁጥር የማውጣት፣ ገቢን የማስታወቅ እና ሌሎችም የታክስ ከፋዮች ግዴታዎች ይኖሩባቸዋል ማለት ነው።
አማራጭ አነስተኛ ግብር
የገቢ ግብር ማሻሻያ አዋጅ ካካተታቸው አዳዲስ ጉዳዮች አንዱ አማራጭ አነስተኛ የግብር ሥርአት ነው። ግብር ከፋዮች ምንም አልሰራንም (ገቢ አላገኘንም) ወይም ስለከሰርን ግብር ልንከፈል አይገባም በማለት ማስታወቅ የተለመደ ነገር ሲሆን በሌላ በኩል ደግሞ ማናቸውም በንግድ ሥራ ላይ የተሰማራ ሰው ለአመታት በኪሳራ ሊቀጥል እንደማይችል ግልፅ ነው። ይህም ግብር ሳይከፍሉ ገቢ በሚያስገኝ ሥራ ላይ የተሰማሩ ሰዎች ሊኖሩ እንደሚችሉ ያስገንዘበናል። ከዚሁ መነሻ ከግብር ለመሸሽ ኪሳራ የሚያስታውቁ ትክክለኛውን ግብር እንዲከፍሉ፣ በትክክል ኪሳራ ያጋጠማቸው ደግሞ መክሰራቸው ሲረጋገጥ የከፈሉት ግብር እንዲካካስ ለማስቻል ሲባል አማራጭ አነስተኛ የግብር ሥርአት እንዲካተት ተደርጓል።
አማራጭ አነስተኛ የግብር ምጣኔን በተመለከተ በአዋጅ ቁጥር 1395/2017 አንቀፅ 2(11) መሠረት ማናቸውም ድርጅት ወይም ሰው ግብር በሚወሰንበት የግብር አመት ከሁሉም የንግድ ሥራ የገቢ ምንጮች ባገኘው ትርፍ ላይ ሊከፍል የሚገባው ግብር በዚሁ የግብር አመት ካገኘው ጠቅላላ ገቢ ከ2.5% (ከሁለት ነጥብ አምስት በመቶ) በታች ከሆነ በአዋጁ በተመለከተው የማስከፈያ ምጣኔ መሠረት አማራጭ አነስተኛ ግብር መክፈል እንደሚኖርበት ተደንግጓል።
በጥሬ ገንዘብ የሚደረግ ግብይት ላይ የተደረገ ገደብ
ሌላኛው የተሻሻለው የገቢ ግብር አዋጅ ይዞት የመጣው ጉዳይ በጥሬ ገንዘቦች የሚደረጉ ግብይቶች ላይ ገደብ ማበጀት ነው። በጥሬ ገንዘብ የሚደረግ ግብይት ስለግብር ከፋዩ ግብይት በቂ መረጃ እንዳይኖር በማድረግ ለታክስ መሰወር ድርጊት በር ከፋች ይሆናል። ይህንንም ለመቀነስ እንዲያስችል ማናቸውም ግብር ከፋይ ወደ ባንክ ሂሳብ ገቢ በሚደረግ ቼክ፣ ወደ ባንክ ሂሳብ ገቢ በሚደረግ የባንክ ድራፍት፣ ከባንክ ሂሳብ ወደ ባንክ ሂሳብ ገንዘብ በማስተላለፍ ወይም በኢትዮጵያ ብሔራዊ ባንክ ፈቃድ በተሰጣቸው የክፍያ መፈጸሚያ መንገዶች ካልሆነ በስተቀር በአንድ ቀን ውስጥ ከአንድ ሰው ጋር በተደረገ ጠቅላላ ግብይት ወይም ከአንድ ግብይት ጋር በተያያዘ የሚፈጸም ክፍያ ወይም ከአንድ ሰው ጋር ከተፈጸመ አንድ ግብይት ወይም ተግባር ጋር የተያያዘ ክፍያ/ግብይቶች ከሃምሳ ሺ (50,000) ብር በላይ በጥሬ ገንዘብ መቀበል አይቻልም። ነገር ግን ይህ ገደብ በመንግሥት መስሪያ ቤቶች፣ በመንግሥት የልማት ድርጅቶች፣ በባንኮች እና በማይክሮ ፋይናንስ ድርጅቶች እንዲሁም የገንዘብ ሚኒስቴር በሚያወጣው መመሪያ መሠረት በተለዩ ሰዎች ወይም ድርጅቶች ላይ ተፈፃሚ እንደማይሆን ከማሻሻያ አዋጁ አንቀፅ 2(28) ድንጋጌ መረዳት ይቻላል።
ማጠቃለያ
በአጠቃላይ የገቢ ግብር ማሻሻያ አዋጅ ቁጥር 1395/2017 ከላይ የተጠቀሱትን ዋና ዋና ማሻሻያዎች ጨምሮ ገቢ ስለሚጣመርበት ሁኔታ፣ ግብር ቀደም ብሎ የሚከፈልበትን አሰራር እና ሌሎች ማሻሻያዎችን አካቶ ወደ ሥራ የገባ ሕግ ነው። ምንጭ የፍትሕ ሚኒስቴር
ታማኝ ፈጣን እና ወቅታዊ መረጃዎችን ለማግኘት የቢሮውን ማኅበራዊ ሚዲያ ማስፈንጠሪያ ይጠቀሙ እናመሰግናለን!!
ዌብሳይት:- aabof.com.et
ፌስቡክ:-https://www.facebook.com/aabof.gov.et?mibextid=ZbWKwL
ቴሌግራም:- https://t.me/AACABOFP
ዩቲዩብ:- youtube.com/channel/UCTPN7Re7T7tp_ekAhVuw2uA
ዋትሳፕ:-https://chat.whatsapp.com/FLSn12vRmsR9JsKUVDWxgtuuuu
አስቸኳይ ማስጠንቀቂያ!
የገቢዎች ሚኒስቴር የታክስ ማጭበርበርን በዘላቂነት ለመከላከል የወሰደው አዲሱ የአሰራር ለውጥ ወደ መጨረሻው ምዕራፍ ተሸጋግሯል።
ከዚህ በታች የተጠቀሱትን ነጥቦች በአጽንኦት ተገንዝበው ተግባራዊ እንዲያደርጉ አቶ ሲሳይ ገዙ የገቢዎች ሚኒስቴር የታክስ ማጭበርበር ምርመራ ቢሮ ኃላፊ አሳስበዋል።
1. የነባር ደረሰኞች ዕድሜ አብቅቷል!
በተለያዩ ማተሚያ ቤቶች ሲታተሙ የቆዩ ነባር ደረሰኞች አገልግሎት የሚያበቃው ታኅሳስ 30 ቀን 2018 ዓ.ም. ነው።
ከጥር 1 ቀን 2018 ዓ.ም. ጀምሮ ልዩ መለያ (QR-Code) የሌለው ማንኛውም ደረሰኝ በሕግ ፊት ዋጋ የለውም።
2. "QR-Code" ያለው ደረሰኝ ብቻ!
ከጥር 1 ቀን ጀምሮ በግብይት ወቅት ጥቅም ላይ መዋል ያለበት በብርሃንና ሰላም ማተሚያ ድርጅት ብቻ የታተመ እና ልዩ መለያ (QR-Code) ያለው ደረሰኝ ብቻ ነው።
ይህ ደረሰኝ የሌላቸው ግብር ከፋዮች ታክሳቸውን ማስላትም ሆነ ማሳወቅ አይችሉም።
3. የማስጠንቀቂያው ጥብቅነት
ተቀባይነት ማጣት፦ ከተጠቀሰው ቀን በኋላ ነባሩን ደረሰኝ ይዘው ወደ ገቢዎች ሚኒስቴር የሚቀርቡ ግብር ከፋዮች ሰነዳቸው ተቀባይነት አይኖረውም።
የሕግ ተጠያቂነት፦ ሕገ-ወጥ ደረሰኝ መያዝ ወይም መጠቀም የታክስ ማጭበርበር ወንጀል ተደርጎ የሚቆጠር ሲሆን፣ በሕግም ያስቀጣል።
4. የታክስ ከፋዮች ግዴታ
ማተሚያ ቤቱ አንድ ብቻ በመሆኑ ሊፈጠር የሚችለውን ወረፋ ግምት ውስጥ በማስገባት፣ ሁሉም ግብር ከፋይ እስከ ጥር 1 ቀን ሳይጠብቅ በአስቸኳይ አዲሱን ደረሰኝ ማሳተም እና ዝግጁ መሆን ይኖርበታል።
ማሳሰቢያ፦ "አላወቅኩም ነበር" ወይም "አላተምኩም" የሚሉ ምክንያቶች ከጥር 1 ቀን በኋላ ተቀባይነት አይኖራቸውም!
ሊንኩን ላይክ በማድረግ ወቅታዊና ጂኦፓለቲካዊ መረጃዎችን በትንታኔ ይኮምኩሙ።
https://t.me/amasadvocatesllp
ለአማራ ክልል መንግሥት ሠራተኞች አስደሳች የሕግ ማሻሻያ ተደርጎላቸዋል
=====================================
አድስ አዋጅ ፀደቀ ህገወጥ ቤቶች ህጋዊ ሊሆኑ ነው!
የአማራ ክልል መሬት ቢሮ አዲስ የገጠር መሬት አጠቃቀም አዋጅ ይፋ አድርጓል።የመንግስት ሰራተኞች በውርስ እና በስጦታ መሬት ማግኘት ይችላሉም ብሏል አዋጁ
አዲሱ የገጠር መሬት አስተዳደርና አጠቃቀም አዋጅ የተካተቱት 6 ወሳኝ ነጥቦች:-
1 በአዲሱ አዋጅ ካሁን በፊት ተግባራዊ በተደረጉ የገጠር መሬት አስተዳደርና አጠቃቀም ህጎች ያልነበሩና የገጠር መሬት ባለይዞታዎችን መብትና ጥቅም ለማስፋት በግል ይዞታ ላይ የለማን የማይንቀሳቀስ ንብረት መሸጥ እና ማስተላለፍ እንዲችሉ ይፈቅዳል።
በዚህም መሠረት በከተሞች ዙሪያ ከሚገኙ አርሶ አደሮች መሬት ገዝተው ቤት የሰሩ ዜጎች በአዲስ ውል ቤታቸውን ህጋዊ ማድረግ ይችላሉ ማለት ነው።
2 የገጠር መሬት ባለይዞታዎች መሬታቸውን በስጦታም ይሁን በውርስ ማስተላለፍ የሚችሉት በገጠር መሬት አዋጅ ለተፈቀደላቸዉ የህብረተሰብ ክፍሎች ነበር፡፡ ይህ ከቤተሰቦቻቸዉ መሬት የማግኘት መብት ሊኖራቸዉ የሚገቡ የህብረተሰብ ክፍሎችን ጥቅም ገድቦ ቆይቷል። በአሁኑ አዋጅ የመንግስት ሰራተኞች ከቤተሰባቸው በዉርስና በስጦታ መሬት ማግኘት እንዲችሉ ይፈቅዳል።
3 በአዲሱ አዋጅ የገጠር መሬት ባለይዞታዎች የይዞታ መብትን ለፈለጉት ሰው በስጦታ፣ በውርስ ማስተላለፍ መብትን ለማንኛውም የህብረተሰብ ክፍል ይፈቅዳል።
4 የገጠር መሬት ይዞታን ለብድር ዋስትና ማስያዣነት በመጠቀም የብድር አገልግሎት ማግኘት የሚቻልበትን ድንጋጌ አካቷል። ይህም የክልሉን አርሶ አደር የብድር አቅርቦት ችግር መፍትሄ የሚሰጥ ነው ተብሏል።
5 በአዲሱ አዋጅ በአስገዳጅ ሁኔታ የመሬት አስተዳደርና አገልግሎት አሰጣጥ ስርአቱ ዲጂታላይዝ መሆን እንዳለበት በግልፅ ተመላክቷል፡፡
6 ለሴቶች፤ ለህፃናት፤ ከቀያቸዉ በጊዜያዊነት ለለቀቁ፤ በህግ ጥላ ስር ያሉ፣ ለህሙማን፤ ለአረጋዊያንና…ወዘተ ጉዳዩን ልዩ ትኩረት በመሰጠት የህግ ከለላና መብት ጥበቃ ሰጥቷል፡፡
Via Wollo Addis
The Ethiopian Federal Advocates Association should take a lesson from this legal blog which is prepared by Mr. Zeray Weldesenbet, Senior Attorney/Advocate, on the topic "A Legal Opinion on the Limits of Delegated Rule-Making Authority Under Article 12(2) of Value Added Tax Proclamation No. 1341/2025", to defend specially the very interest of many Advocates who don't meet the legal threshold to be registered for VAT.
By Zeray Weldesenbet (Advocate)
Legal Issue:
The preamble of the Directive on Registration for Value Added Tax (Directive No. 1104/2025) states: "…. NOW THEREFORE, the Ministry of Finance hereby issues this Directive pursuant to the power vested to it under Article 12 sub-article (2) of the Value Added Tax Proclamation No. 1341/2025 ".
This raises the following questions:
(1) Does Article 12(2) of Value Added Tax (VAT) Proclamation No. 1341/2025 empower the Ministry of Finance to impose categorical VAT registration, irrespective of annual turnover?
(2) If the Ministry does have this power, what is the policy goal behind granting such authority, particularly given that non-professional businesses are required to register based on their annual turnover?
(3) What is the Ministry's justification for imposing categorical VAT registration upon all professional services providers?
This legal note briefly examines the scope of the rule-making power granted to the Ministry of Finance under Article 12(2) of VAT Proclamation No. 1341/2025, its objective, and other related matters. This note applies three standard canons of legal interpretation to Article 12(2) of VAT Proclamation No. 1341/2025, in addition to other relevant factors. In this Note, I have touched on the legal issue with the aim of providing a starting point for further discussions rather than a comprehensive answer.
Legal Analysis:
1. The Plain Meaning/Literal Rule of Legal Interpretation
Understanding what the law is depends inescapably on the texts and its structure. Based on this principle, Article 12(2) of VAT Proclamation No. 1341/2025 states:
"The registration threshold is 2,000,000 Birr or such other amount as specified in the Directive to be issued by the Ministry."
The controlling phrase under this provision is "or such other amount" (of money). The word "amount" (of money) unambiguously refers to a numerical, financial value. It does not state "such other criteria," "such other categories," or "such other persons." “Amount” in ordinary English also means a sum of money. It does not, under its plain meaning, extend to categories of taxpayers, persons, or conditions. Thus, this provision grants the Finance Ministry the specific power to substitute the monetary figure of 2,000,000 Birr for another monetary amount (e.g., 1,500,000 or 3,000,000 Birr). It is a power to adjust the quantitative benchmark, not to redefine the qualitative nature of the obligation itself, which is fundamentally based on exceeding a financial threshold.
The Amharic version of Article 12(2) of the VAT Proclamation reinforces this interpretation. The Amharic version of Article 12(2) of VAT Proclamation No. 1341/2025 states:
"፪/ ለተጨማሪ እሴት ታክስ የመመዝገብ ግዴታ የሚኖረው ብር ፪ ሚሊዮን (ሁለት ሚሊዮን ብር) የጠቅላላ አቅርቦት ድምር ሲኖር ወይም ሚኒስቴሩ በመመሪያ የሚወስነው ሌላ ታክስ የሚከፈልበት የአቅርቦት የገንዘብ መጠን ያለው ሰው ነው፡፡”
The controlling phrase of the Amharic text is "ወይም ሚኒስቴሩ በመመሪያ የሚወስነው ሌላ ታክስ የሚከፈልበት የአቅርቦት የገንዘብ መጠን" (another monetary value of supply on which tax is paid) centers on the financial measure ("ሌላ ታክስ የሚከፈልበት የአቅርቦት የገንዘብ መጠን"), not on creating new taxpayer categories. Under the Amharic version, the term "የገንዘብ መጠን" (amount of money) unequivocally refers to a numerical, financial value.
The term "or" ("ወይም") in this provision is also crucial. The disjunctive "or" presents two alternatives of the same kind: one monetary threshold or another. It does not grant the power to replace a financial test with a categorical one. It means the phrase "or such other amount" is directly linked to and is an alternative to "2,000,000 Birr." "2,000,000 Birr" is a clear financial registration threshold determined by the legislature. Hence, "or such other amount" must be interpreted as another financial registration threshold (e.g., 1,500,000 Birr or 3,000,000 Birr), maintaining the same nature as the original concept. It is not surrounded by words like "category," "sector," or "profession," which would indicate a broader power to discriminate between types of businesses.
Consequently, the delegated power is solely to alter the monetary figure, not to introduce sector-specific registration rules. Therefore, a directive mandating registration based solely on a business category (e.g., all lawyers or doctors) and not on financial turnover would constitute a fundamental change to the registration rule, not an adjustment of the "amount." Such an action would be ultra vires under this specific article.
2. The Contextual Legal Interpretation Rule (Noscitur a Sociis)
The phrase "such other amount" is directly linked to and presented as an alternative to "2,000,000 Birr". Since "2,000,000 Birr" is a financial registration threshold, its counterpart, "such other amount," must be interpreted as being of the same character, another financial registration threshold. It is not surrounded by words suggesting a power to discriminate by sector or profession. This contextual interpretation confirms that the delegated rule making power is solely to alter the universal monetary figure applicable to all taxpayers without any sectorial or otherwise distinction among taxpayers. Moreover, this interpretation is corroborated by the structure of the Proclamation.
The definitions under Articles 2(28) and 2(33)-(34) and compulsory registration provisions in Article 12 of the VAT Proclamation solidify that the only path to mandatory registration is exceeding a monetary amount. The structure of the law is entirely based on financial benchmarks. Due to this, introducing a third, non-financial path (categorical registration obligation) would disrupt this logical structure and create a conflict between a financial registration threshold and a non-financial registration threshold. This would be an arbitrary distinction between professional services providers and non-professional services providers and legally unsustainable distinction.
3. The Principle of Legality in Tax Law & Hierarchy of Norms
An action taken without a clear legislative mandate is ultra-vires and is therefore invalid. In principle, tax obligations must be created by the legislature according to Articles 55(1), 57, 71(2), 77(13) and 100 of FDRE Constitution. This is the highest source of law and establishes that the power to levy taxes resides with the parliament. This is the ultimate hierarchy of norms.
In addition to this, a fundamental principle of tax law is that an administrative agency cannot create a new tax liability without a clear and specific legislative mandate according to Articles 2(2), 4(1) and 50 of Federal Administrative Procedure Proclamation No. 1183/2020. Article 12(2) is a narrow delegation to adjust a pre-defined financial criterion, not an authorization to invent a new categorical criterion for liability. It is not an authorization for the Ministry to invent a new categorical criterion for liability. To impose a VAT registration requirement based purely on business category, a specific mandate would be required within the Proclamation itself, or the Proclamation would need to be amended by Parliament.
In addition to this, a Directive, as subordinate legislation, cannot override or contradict the fundamental structure of the liability regime established by the parent Proclamation, as provided by Article 50(1)(c) of Federal Administrative Procedure Proclamation. To do so violates the principle of legality and the constitutional hierarchy of laws. The Directive must operate within the framework of FDRE Constitution and the Proclamation. Creating an entirely new criterion for tax liability is a legislative act that sits with the parliament, not the administrative agency. Thus, the constitutional hierarchy of norms dictates that a Directive, as subordinate legislation, cannot alter the fundamental structure of the liability regime established by the Proclamation. This is not a legal interpretation, but a constitutional and legal principle concerning the separation of powers between the legislative and executive.
4. The Purpose of the Law (Teleological Interpretation)
Under the Ethiopian VAT Proclamation, the policy objectives of the VAT registration threshold are generally twofold. The primary purpose is to reduce the administrative burden on both the tax authority and small and medium businesses. It achieves this by: (A) Exempting very small businesses from the complexities of VAT accounting, invoicing, and filing returns. (B) Allowing the tax authority to focus its compliance resources on larger businesses that collect the majority of VAT revenue. (C) Preventing the tax system from stifling the growth of micro enterprises and startups. The secondary purposes are to foster the growth of small and medium enterprises, promote progressivity and equity in an indirect tax system, and improve economic efficiency through the rationalization of resources.
By exempting small businesses from VAT, the government significantly reduces their compliance costs. This allows entrepreneurs to focus their limited resources on growth rather than tax administration, enabling them to retain more capital for reinvestment or savings. Furthermore, businesses below the threshold gain a competitive advantage by not charging their customers the 15% VAT and avoid potential cash flow problems. The threshold also acts as a "safe harbor," encouraging informal micro-businesses to eventually transition into the formal economy as they grow. Given these administrative, policy, and economic purposes, adjusting the threshold up or down serves clear goals (e.g., raising it to protect more businesses or lowering it to widen the tax base). Thus, the registration threshold is a fundamental part of the Ethiopian VAT system.
However, eliminating this threshold for a specific sector directly contravenes these stated purposes. It would impose the full compliance burden, specifically the costs the threshold was designed to avoid, on a small sole practitioner with minimal turnover, while exempting a much larger business in a different sector that remains above the general turnover threshold. This creates an arbitrary discrimination and unfair distinction that undermines the policy rationale for the registration threshold itself.
5. Corroboration from Article 17 (Cancellation of Registration)
The provisions of Article 17 of the VAT Proclamation (Cancellation of Registration) further support this interpretation. Article 17 provides a mechanism for a registered person to apply for cancellation if their annual taxable supplies "are below the registration threshold." This right is integral to a threshold-based system. This right is a fundamental feature of a threshold based system. A directive that eliminates the financial threshold for a category of taxpayers would effectively and unlawfully sn**ch this statutory right away from all professional service providers, contradicting a threshold-based system established by the Proclamation itself. A Directive cannot lawfully nullify a right explicitly granted by the primary legislation. A Directive for categorical registration irrespective of turnover would create a glaring inequality between professional services providers and non-professional services providers and directly contradict the clear right granted by Article 17 of the Proclamation. Hence, the right to cancel registration is incompatible with categorical registration. Therefore, Article 17 of the VAT Proclamation No. 1341/2025 reinforces the interpretation that the Ministry of Finance cannot use Article 12(2) of the VAT Proclamation to issue a Directive that requires all professional service providers to register for VAT regardless of their annual turnover.
6. Rebuttal of the Ministry's Justifications and Ultra-Vires Action
The foregoing interpretation is further bolstered when considering the Ministry's justifications, which are fundamentally flawed for the following reasons. The Ministry’s justification, as stated in the preamble, is to ensure “fairness” by requiring VAT registration for “any person providing professional services whose annual turnover is less than 2 million birr and who is not classified as a Category ‘B’ taxpayer.” The Ministry's logic is that such professionals are already classified as Category ‘A’ taxpayers under Article 50(4)-(5) of the Income Tax Proclamation (as they are excluded from the Category ‘B’ turnover threshold) and are therefore already subject to rigorous accounting standards. It is deemed "unfair" that they escape the VAT net due to the turnover threshold, while a larger business in a different sector must register. These justifications are fundamentally flawed for the following reasons:
Firstly, ultra vires action and strict interpretation of taxing provisions: The principle of strict interpretation of taxing provisions (in dubio contra fiscum) requires that any ambiguity in a law imposing a tax burden be resolved in favor of the taxpayer. This principle precludes reading a broad categorical power into the narrow phrase “such other amount” in Article 12(2) of the VAT Proclamation. The Ministry's power is limited to specifying a different numerical value for the turnover threshold. It does not grant the authority to replace the entire turnover-based registration system with a new set of criteria based on a taxpayer's profession or their classification under a completely different tax law. By attempting to do so, the Ministry has acted ultra vires, beyond the powers granted to it by the Proclamation. Secondly, the flawed premise of the Directive: The Ministry’s justification, as stated in the preamble, is based on an incorrect legal premise. It asserts the necessity to register professionals who are "not classified as a Category 'B' taxpayer," implying they are necessarily Category A. This is a fundamental error. A professional with an annual turnover below 2 million Birr is not automatically excluded from Category B classification under the Income Tax Proclamation (as amended). The Proclamation does not universally classify all professionals as Category A; such a classification would be determined by their specific circumstances and compliance with the definitions and thresholds within the Income Tax law itself. Therefore, the entire foundational justification for the Directive is built on an incorrect assumption of law, rendering it arbitrary and legally unsound.
Thirdly, conflation of separate legal regimes and arbitrary targeting: Obligations under the Income Tax Proclamation are separate and distinct from obligations under the VAT Proclamation. The Ministry's attempt to use a directive under the VAT law to compel registration based on a perceived status in the income tax regime is a clear conflation of two independent legal frameworks. This leads to arbitrary and unfair treatment. The Directive singles out a specific profession for a harsher treatment—denying them the universal turnover threshold benefit available to all other sectors. This is the antithesis of fairness, which in tax law is achieved through the neutral and universal application of clear, predictable rules. Fourthly, a matter for primary legislation: The administrative impracticality of defining "professional service providers" and the significant policy shift from a general turnover rule to a targeted occupational one underscore that this change is a matter for primary legislation to be debated and enacted by Parliament. It is not a matter to be decided by administrative directive, especially under a delegated rule-making power only granted to change an "amount."
For these reasons, Directive No. 1104/2025 is apparently unlawful. It exceeds the Ministry's delegated rule-making authority, is based on a flawed legal premise, unfairly targets a specific profession, and attempts to enact a major policy shift that should be reserved for primary legislation. The Directive No. 1104/2025 should be struck down, and the original, clear turnover threshold regime of Article 12 of the VAT Proclamation should prevail.
Furthermore, the above legal interpretation is bolstered by overarching legal principles. The principle of strict interpretation of taxing provisions (in dubio contra fiscum) requires that any ambiguity in a law imposing a tax burden be resolved in favor of the taxpayer. This principle precludes reading a broad categorical power into the narrow phrase “such other amount” in Article 12(2) of the VAT Proclamation. Even if the phrase were considered ambiguous, this principle dictates that the ambiguity must be resolved against the Ministry’s authority to impose a broader categorical obligation. The benefit of the doubt afforded to the taxpayer means the Ministry’s rule-making power under this clause is limited to adjusting the numerical threshold, not replacing the turnover-based system with an entirely new set of criteria. Furthermore, the administrative impracticality and arbitrariness inherent in defining ‘professional service providers’ for this purpose underscore that such a significant policy shift is a matter for primary legislation debated and enacted by Parliament, not an administrative directive issued by the Ministry. Hence, the Ministry's directive represents a significant overreach of its delegated authority and is based on a flawed and arbitrary interpretation of the law.
7. Distinguishing Income Tax Obligations From VAT Obligations
Some may argue that since Article 50(4)-(5) of the Income Tax Proclamation No. 979/2016 (as amended) states that all professional services providers shall maintain books of account, they shall be registered for VAT without a registration threshold. This argument is a non sequitur and legally unsound. Article 50(4)-(5) of the Income Tax Proclamation (as amended) deals exclusively with income tax obligations and is completely separate from the VAT registration rules under Proclamation No. 1341/2025. The inapplicability of the Income Tax Proclamation (as amended) is clear. It is legally unsound to conclude that all professionals are excluded from presumptive tax so that they must be VAT-registered. A business could be a professional but have a turnover below the VAT threshold. It would be excluded from presumptive tax under 50(4)(a) but would not be forced to register for VAT. A business could be a retailer (not a professional) but have a turnover above the VAT threshold. It would be excluded from presumptive tax under 50(4)(b) because it is VAT-registered. Thus, Article 50 of the Income Tax Proclamation is irrelevant. Article 50(4)-(5) of Income Tax Proclamation No. 979/2016 imposes stricter income tax accounting rules on professionals. It deals with calculating net profit, not VAT on turnover. That means, it does not mention VAT, alter VAT thresholds, or provide a legal basis for the Ministry's action under the VAT Proclamation. This conflation of two distinct tax regimes is a critical legal error.
Conclusion and Recommendation
Conclusion: The Ministry of Finance may issue a Directive to increase or decrease the universal financial registration threshold (the 2,000,000 Birr figure). The Ministry's power under Article 12(2) of the VAT Proclamation is limited to issuing a Directive that changes the numerical value of the registration threshold for all taxpayers. It cannot use this provision to issue a Directive that requires all professional service providers to register for VAT regardless of their annual turnover. The Ministry of Finance may not use Article 12(2) of the VAT Proclamation to eliminate the financial registration threshold for a specific sector and mandate categorical VAT registration. To require all professional service providers to register irrespective of turnover, the government would need to amend the VAT Proclamation itself through Parliament to include such a specific provision.
Recommendation: If the policy goal is to mandate VAT registration for all providers of professional services irrespective of turnover, the government must pursue one of two lawful pathways:
1. Amend the VAT Proclamation: Parliament can amend Article 12 and other related provisions of the Proclamation to explicitly state that "providers of professional services must register for VAT regardless of their annual turnover."
2. Seek Broader Delegated Authority: Parliament could amend Article 12(2) to grant the Ministry of Finance the specific power to "define categories of taxpayers who must register irrespective of the financial threshold."
A Directive issued under the current Article 12(2) attempting to achieve this goal would be susceptible to legal challenge and struck down as ultra vires and unlawful.
-------
Footnotes:
1. Antonin Scalia and Bryan Garner, Reading Law: The Interpretation of Legal Texts (2012), PP. 3 and 567.
2 . In legal interpretation, the disjunctive "or" is a conjunction that presents alternatives, indicating that only one of the connected items, conditions, or possibilities may apply.
3. See Federal Administrative Procedure Proclamation No. 1183/2020, Arts. 2(2), 4(1), 50.
4 . The delegation of rule-making authority to administrative agencies is a subject of constitutional challenge. The FDRE Constitution is silent on permitting this delegation, unlike the explicit authority for issuing regulations granted to the Council of Ministers under Article 77(13).
5 . The principle of legality, within the framework of the hierarchy of norms, requires that lower-level legislation must conform strictly to higher-level legislation and must not contain contrary provisions.
6 . The principle of legality is essential to guard taxpayers from intrusive actions of an overreaching executive branch.
7. See FDRE Constitution, Art. 25 (enshrining the principle of equality and non-discrimination).
8. See 4 Mertens Law of Federal Income Taxation § 3:29 (2024).”
By Zeray Weldesenbet (Advocate)
Click here to claim your Sponsored Listing.
Category
Website
Address
Addis Ababa
Opening Hours
| Monday | 08:30 - 17:30 |
| Tuesday | 08:30 - 17:30 |
| Wednesday | 08:30 - 17:30 |
| Thursday | 08:30 - 17:30 |
| Friday | 08:30 - 17:30 |
| Saturday | 08:30 - 17:30 |