Gebeya

Gebeya

Share

Here you can find Accessories for Men and Women,Watch,Neck chain,mobile devices,mobile covers,bands

Photos 27/07/2020

Gebeya News 🗞📰

ከሀሰተኛ መረጃ እራሳችሁን ጠብቁ!

'የመሰቦ ሲሚንቶ ፋብሪካ' ዋና ስራ አስከያጅ አቶ ክብረአብ ተወልደ በቤታቸው ውስጥ እያሉ ከ 30 ሚልዮን ብር ካሽ ጋር በቁጥጥር ስር እንደዋሉ ተደርጎ በማህበራዊ ሚዲያ የሚሰራጨው መረጃ #ሀሰተኛ ነው።

አቶ ክብረአብ ተወልደ ፥ መረጃው ውሸት እንደሆነ፣ እሳቸው በስራ ላይ እንደሚገኙና አሁንም ወደፊትም እንዲህ አይነት ነገር እንደማይኖር በራሳቸው እርግጠኛ መሆናቸውን ለአሶሼትድ ፕሬስ ጋዜጠኛው ኤልያስ መሰረት ተናግረዋል።

26/07/2020

ሰሜን ኮሪያ 'የመጀመሪያውን' የኮሮናቫይረስ ተጠርጣሪ ማግኘቷን አስታወቀች
*********************
ሰሜን ኮሪያ በአገሪቱ የመጀመሪያው የተባለውን በኮሮናቫይረስ የተጠረጠረ ሰው ማግኘቷን አስታወቀች።
በሽታው እንዳለበት የተጠረጠረው ግለሰብ ከሦስት ዓመት በፊት ወደ ደቡብ ኮሪያ ከድቶ ሄዶ የነበረ ሲሆን በቅርቡ በድንበር በኩል ወደ ሰሜን ኮሪያ ከተመለሰ በኋላ የወረርሽኙ ምልክቶች የታዩበት መሆኑን ቢቢሲ የአገሪቱን መንግሥት የዜና አገልግሎት ጠቅሶ ዘግቧል።
ይህንንም ተከትሎ የአገሪቱ መሪ ኪም ጆንግ-ኡን ከፍተኛ ባለሥልጣኖቻቸውን ሰብስበው ከደቡብ ኮሪያ ጋር በምትዋሰነው የድንብር ከተማዋ ኬሶንግ ላይ የእንቅስቃሴ ገደብ እንዲጣል ማድረጋቸው ተገልጿል።
ለመረጃ ዝግ የሆነችው ሰሜን ቀደም ሲል በኮሮናቫይረስ የተያዘ ሰው እንደሌለባት ስታሳውቅ ብትቆይም፣ ተንታኞች ግን ሊሆን እንደማይችል ሲገልጹ ቆይተዋል።
በትናንትናው ዕለት በተካሄደው የአገሪቱ ከፍተኛ ባለሥልጣናት አስቸኳይ ስብሰባ መሪው ኪም ጆንግ-ኡን የቫይረሱን ስርጭት ለመቆጣጠር "ከፍተኛ የአስቸኳይ ጊዜ ሥርዓት" እንዲዘረጋ ማዘዛቸው ተወስቷል።
መሪው ኪም ጆንግ-ኡን በበሽታው የተጠረጠረው ግለሰብ በከፍተኛ ጥበቃ ስር ባለው የድንበር አካባቢ ከደቡብ ወደ ሰሜን ኮሪያ እንዴት አልፎ ሊገባ እንደቻለ እንዲመረመር ያዘዙ ሲሆን፤ ተጠያቂ የሚሆኑ ሰዎች ላይ "ከባድ የቅጣት እርምጃ" እንዲወሰድባቸው ማዘዛቸውም ነው የተነገረው።
ደቡብ ኮሪያ በበኩሏ በተመሳሳይ ጊዜ ምንም አይነት ሕገ ወጥ የድንበር ማቋረጥ ክስተት እንዳልነበረ ማስታወቋ ተገልጿል።
ከስድስት ወራት በፊት ቫይረሱ በዓለም ዙሪያ መስፋፋት በጀመረበት ጊዜ ሰሜን ኮሪያ ድንበሮቿን ዘግታ በሺህዎች የሚቆጠሩ ሰዎችን ወደ ለይቶ ማቆያ ውስጥ አስገብታለች።
በዚህ ወር መጀመሪያ ገደማ ላይ መሪው ኪም ጆንግ-ኡን አገራቸው በኮሮናቫይረስ ላይ "አንጸባራቂ ስኬት" እንደተቀዳጀች አሳውቀው ነበር ነበር ብለዋል።

26/07/2020

Gebeya News 📰🗞

በዓለም አቀፍ ደረጃ በኮሮናቫይረስ የተያዙ ሰዎች ቁጥር 16 ሚሊዮን ተሻገረ
************************
በዓለም አቀፍ ደረጃ በኮሮናቫይረስ የተያዙ ሰዎች ቁጥር 16 ሚሊየን በላይ ደርሷል።
ከእነዚህ ሰዎች መካከል 10 ሚሊዮን ገደማ የሚሆኑት ከበሽታው ማገገማቸውን ከወርልዶሜትርስ ዶት ኢንፎ የተገኘው መረጃ ያመለክታል።
በበሽታው እስከ ዛሬ ከሰዓት ድረስ ከ643 ሺህ በላይ ሰዎች ሕይወታቸውን አጥተዋል።
በዓለም አቀፍ ደረጃ አሜሪካ 4 ሚሊዮን 250 ሺህ በላይ፣ ብራዚል 2 ሚሊየን 350 ሺህ ገደማ እንዲሁም ሕንድ 1 ሚሊየን 360 ሺህ በላይ በቫይረሱ የተያዙ ሰዎች በማስመዝገብ ቀዳሚነቱን ይዘዋል።
በአፍሪካ አህጉር በኮሮናቫይረስ የተያዙ ሰዎች ቁጥርም 815 ሺህ አልፏል።
ከዚህም ቁጥር ውስጥ ደቡብ አፍሪካ ከ422 ሺህ ገደማ፣ ግብጽ ከ91 ሺህ በላይ እና ናይጀሪያ 40 ሺህ ገደማ በቫይረሱ የተያዙ ሰዎች በማስመዝገብ ከአንድ እስከ ሦስት ያለውን ደረጃ ይዘው ይገኛሉ።

23/07/2020

Gebeya News 🗞📰

የኢንተርኔት መቋረጥና የትራንስፖርት አገልግሎት...

'ዛይራይድ' የትራንስፖርት አገልግሎት ሰጪ ድርጅት በሀገሪቱ በተከሰተው የፀጥታ ችግር ሳቢያ ኢንተርኔት በመቋረጡ በ2 ሳምንት ግማሽ ሚሊዮን ብር (500,000 ብር) ገቢ ማጣቱን ለሸገር ኤፍ ኤም 102.1 ተናግሯል።

23/07/2020

Welcome back Ethiopia 🇪🇹😘🥰🇪🇹

26/06/2020

በመደጋገፍ፣ በሥራና በፅናት የሚገነባ ሀገር እንጂ በወሬ የሚገነባ ከተማም፤ ሀገርም የለምና ጸንተን ሀገራችንን እንገነባለን።

Takele Uma Banti

25/06/2020

Gebeya News 📰🗞

በአፍሪካ የኮሮናቫይረስ የመጀመሪያው የክትባት ሙከራ ተጀመረ፡፡
ባሕር ዳር፡ ሰኔ 18/2012 ዓ.ም (አብመድ) አምስት የአፍሪካ ሀገራት በከፍተኛ ደረጃ የክትባት ሙከራ አቅም መገንባታቸው ታውቋል፡፡
በአፍሪካ የኮሮናቫይረስ ክትባት በሙከራ ደረጃ ትናንት ሰኔ 17/2012 ዓ.ም እንደተጀመረ ሲ ጂ ቲ ኤን ዘግቧል፡፡ በእንግሊዝ ኦክስፎርድ ዩኒቨርሲቲ በልጽጎ የተሰራው ክትባት በደቡብ አፍሪካ፣ እንግሊዝና ብራዚል መጠነ ሰፊ ሙከራ እየተደረገበት እንደሆነ ተዘግቧል፡፡ ከጆሃንስበርግ በክትባት ሙከራው በበጎ ፈቃደኝነት የተሳተፈው ጁኒየር ሙህሎንጎ ''በትንሹ ብፈራም በክትባቱ ምን እንደሚከሰት ለማወቅ እሻለሁ፤ ይህም ለጓደኞቼና ለሌሎች በጥናቱ ምን እንደተካሄደ መናገር ያስችለኛል'' ብሏል።
ካሜሮን፣ ዩጋንዳ፣ ታንዛኒያ፣ ደቡብ አፍሪካና ኬንያ በከፍተኛ ሁኔታ ክሊኒካዊ የክትባት ሙከራ አቅም መገንባታቸውን በደቡብ አፍሪካ የኮሮናቫይረስ የሚኒስትሮች አማካሪ ኮሚቴ ሊቀ መንበር ሳሊም አብዱል ካሪም ተናግረዋል። ሌሎች ከሰሃራ በታች ያሉ በርካታ የአፍሪካ ሀገራትም ክሊኒካዊ የሙከራ አቅም እንዳላቸው በእንግሊዝ የኅብረተሰብ ጤና ፈጣን ምላሽ ሰጪ የድጋፍ ቡድን ዳይሬክተር ዳንኤል ቦስች አስታውቀዋል፡፡
1 ነጥብ 3 ቢሊዮን ሕዝብ ያላት አፍሪካ በዓለም አቀፍ ደረጃ ከኮሮናቫይረስ ክትባት ጋር በተገናኘ የአቅርቦት መሰናክሎች እንዳይጋረጡባትና እንዳትገፋ የሚሉ ስጋቶች አሉ። የአዓም ጤና ድርጅት ዋና ዳይሬክተር ዶክተር ቴድሮስ አድሃኖም ደግሞ ማንኛውም ቀዳሚ የቫይረሱ ክትባት አቅርቦት በእጅጉ በሚያስፈልግበት አካባቢ እንጂ ገንዘብ በመክፈል አቅም መሆን እንደሌለበት እያስታወቁ ነው፡፡
ቻይናም የኮሮናቫይረስ ክትባት ካገኘች የአፍሪካ ሀገራትን ከቀዳሚ ተጠቃሚዎች መካከል እንደምታደርግ ማስታወቋ ይታወሳል፡፡
በኪሩቤል ተሾመ

23/06/2020

Gebeya News 📰🗞

ተመድ ኢትዮጵያ፣ ሱዳንና ግብፅ በግድቡ ዙሪያ ያለቸውን ልዩነት በውይይት እንዲፈቱት አሳሰበ

የተባበሩት መንግስታት ድርጅት ኢትዮጵያ፣ ሱዳንና ግብፅ በታላቁ የኢትዮጵያ ህዳሴ ግድብ ዙሪያ ያለቸውን ልዩነት በጋራ ውይይት እንዲፈቱት አሳሰበ።
በግብፅ በግድቡ ዙሪያ እየተደረገ ያለው ድርድር ከስምምነት ላይ ሳይደረስ የውሃ ሙሌት እንዳይጀመር ስትል ለተባበሩት መንግስታት የፀጥታው ምክር ቤት ደብዳቤ ማስገባቷ ይታወሳል።

ሀገሪቱ የፀጥታው ምክር ቤት በጉዳዩ ላይ መክሮ የውሳኔ ሀሳብ ያሳልፋል ብላ ብትጠብቅም፤ የዲፕሎማቲክ ምንጮች እንዳስታወቁት ግን ምክር ቤቱ በጉዳዩ ላይ ምንም አይነት ስብሰባ እንደማያደርግ እና የውሳኔ ሀሳብ እንደማያሳልፍ አረጋግጠዋል።
ይልቁንም ሀገራቱ ልዩነታቸውን በጋራ እንዲፈቱ በደብዳቤ ብቻ እንደሚያሳውቅም ዲፕሎማቲክ ምንጮቹ አስታውቅዋል።
ታላቁ የኢትዮጵያ ህዳሴ ግድብን አስመልክቶ ግብፅ ለተባበሩት መንግስታት ድርጅት የፀጥታው ምክር ቤት ጥያቄ ማቅረቧን ተከትሎ ኢትዮጵያ ያላትን አቋም በድጋሚ ለምክር ቤቱ ግልጽ አድርጋለች።
የውጭ ጉዳይ ሚኒስትር አቶ ገዱ አንዳርጋቸው ለፀጥታው ምክር ቤት በላኩት ደብዳቤም፥ ኢትዮጵያ እየገነባች ያለችው ግድብ የታችኛውን የተፋሰስ አገር እንደማይጎዳ እና የሰላም እና ፀጥታ ስጋትም አለመሆኑን በድጋሜ አረጋግጠዋል።
ሱዳንም፤ የታላቁ የኢትዮጵያ ህዳሴ ግድብ ጉዳይ በድርድር ሂደት ላይ እያለ ግብፅ ጉዳዩን ወደ ተባበሩት መንግስታት ድርጅት የፀጥታው ምክር ቤት መውሰዷን እንደማትቀበል መግለጿ ይታወቃል።
የተባበሩት መንግስታት ድርጅት ቃል አቀባይ ስቴፋን ጃሪክም በእለታዊ መግለጫቸው ህዳሴ ግብድን አስመልክቶ ለኢትዮጵያ፣ ሱዳንና ግብፅ መልእክት አስተላልፈዋል።
ቃል አቀባዩ በመግለጫቸው፥ ሶስቱ ሀገራት በታላቁ የኢትዮጵያ ህዳሴ ግድብ ዙሪያ ያለቸውን ልዩነት በጋራ በመምከር መፍታት ይጠበቅባቸዋል ብለዋል።
ሀገራቱ በአውሮፓውያኑ በ2015 በግድቡ ዙሪያ በፈረሙት የመርሆዎች ስምምነትን በመከተል ለልዩነቶቻቸው መፍትሄ ማበጀት ይገባቸዋል ሲሉም አሳስበዋል።
ምንጭ፦ cgtn.com

23/06/2020

Gebeya News 📰🗞

ከግብፅ የተቃጡ የሳይበር ጥቃቶችን ማክሸፉን ኤጀንሲው አስታወቀ
አዲስ አበባ፣ ሰኔ 16፣ 2012 (ኤፍ.ቢ.ሲ) የኢንፎርሜሽን መረብ ደህንነት ኤጀንሲ ሰኔ 10፣ 12 ፣ 13 እና 14/2012 ዓ.ም መቀመጫቸዉን ግብፅ ያደረጉ የሳይበር ወንጀለኞች በኢትዮጵያ የኢኮኖሚያዊ እና ፖለቲካዊ ጫና ለመፍጠር የተቃጡ የሳይበር ጥቃቶችን ማክሸፉን አስታውቋል።
የሳይበር ጥቃት ሙከራው የተቃጣው ሳይበር ሆሩስ ግሩፕ፣ አኑቢስ ዶት ሃከር እና ሴኪዩሪቲ ባይ ፓስ በተባሉ የሳይበር አጥቂዎች አማካይነት መሆኑን ኤጀንሲው ገልጿል።
ወንጀለኞቹ ለረጅም ጊዜ ሲዘጋጁ የቆዩ እና ኤጀንሲው ሲከታተላችው የነበሩ ሲሆን፥ በይበልጥ አርብ ሰኔ 12/2012 እና ቅዳሜ ሰኔ 13/2012 ከፍተኛ የሚባል የሳይበር ጥቃት ሙከራዎች ማድረጋቸውን ኤጀንሲው ገልጿል።
በዚህ ጊዜ ዉስጥ የ13 የመንግስት፣ 4 መንግስታዊ ያልሆኑ ተቋማትን የድረ-ገጽን የማስተጓጎል ሙከራ ማድረጋቸውን አስታውቋል።
የሳይበር ጥቃት ሙከራው በሀገሪቱ የመንግስት አገልግሎት ሰጪ ተቋማት፣ የደህንነት መስሪያ ቤቶች እና የግል ድርጅቶች ድረ-ገጽ ላይ ያነጣጠረ ነበር።
ሳይበር ሆሩስ ግሩፕ፣ አኑቢስ ዶት ሃከር እና ሴኪዩሪቲ ባይ ፓስ የሳይበር ጥቃት አድራሽ ቡድኖች ሃላፊነቱን የወሰዱ ሲሆን፥ ዋና አላማቸዉም ከህዳሴው ግድብ ዙሪያ በተለይ በውሃ አሞላል ጋር በተያያዘ ሁሉን አቀፍ ተጽእኖ በሀገሪቱ ላይ ለመፍጠር በማሰብ እንደፈጸሙት ገልጸዋል።
የሳይበር ጥቃት የተሰነዘረባቸው ተቋማት አብዛኛዎቹ በድረ-ገጽ ግንባታ ሂደት ደህንነታችው ታሳቢ ያላደረጉ ተቋማት፤ በቀጣይነት የደህንነት ፍተሻ ያላደረጉ እና ከፍተኛ የሳይበር ደህንነት ተጋላጭነት የነበረባቸው መሆኑንም ኤጀንሲው አረጋግጧል።
ኤጀንሲው አስቀድሞ ቅድመ ዝግጅት በማድረጉ ምክንያት እና ይህን መጠነ ሰፊ የሳይበር ጥቃት መከላከል ባይችል ኖሮ ጥቃቱ በሀገሪቱ ኢኮኖሚያዊ፣ ፖሊቲካዊ እና ስነ ልቦናዊ ጉዳት ሊያስከትል ይችል እንደነበርም ገልጿል።
በመከላከሉም ሊደርሱ የሚችሉ ከፍተኛ አደጋዎችን ማስወገድ መቻሉን እና ይህንንም ተግባር አጠናክሮ እንደሚቀጥልበት ማሳወቁንም ከኤጀንሲው ያገኘነው መረጃ ያመለክታል።
በቀጣይም መሰል ጥቃቶች በስፋት፣ በረቀቀ መንገድ እና ከተለያዩ ስፍራ ሊሰነዘር እንደሚችል ግምት ውስጥ በማስገባት ግለሰቦችም ሆኑ ተቋማት .et domain ከመጠቀማቸው በፊት የድረ-ገጻቸውን ደህንነት አረጋግጠው እንዲጠቀሙ፤ ራሳቸውን ከሳይበር ደህንነት ተጋላጭነት ለመከላከል እና አስፈላጊውን የጥንቃቄ እርምጃዎችን መውሰድ እንደሚኖርባቸው አሳስቧል።
ተቋማት ከኤጀንሲው ጋር በመተባበር ያለባቸውን የደህንነት ተጋላጭነት መድፈን እንዳለባችው እና የተለያዩ የሳይበር ደህንነት ጥቃት ሙከራ ሲያጋጥማቸውም ሆነ ሙያዊ ድጋፍ ሲያሻቸው ለኤጀንሲው በማሳወቅ አስፈላጊውን ትብብርና ድጋፍ ማግኘት እንደሚችሉ አስታወቋል።
ባለፉት ሁለት ቀናት ትብብር ላደረጉልን ተቋማት እና ግለሰቦች በተለይ ለኢትዮ ቴሌኮምና ለኢኖቬሽን እና ቴክኖሎጂ ሚኒስቴር ኤጀንሲው ምሰጋና አቅርቧል።

23/06/2020

Gebeya News 🗞📰

ሊደደርሱ የነበረውን የሳይበር ጥቃቶችን ማክሸፍ ተችሏል-- ኢመደኤ

የኢንፎርሜሽን መረብ ደህንነት ኤጀንሲ (ኢመደኤ) ሰኔ 10፣ 12 ፣ 13 እና 14/2012 ዓ.ም መቀመጫቸዉን ግብጽ ያደረጉ የሳይበር ወንጀለኞች በኢትዮጵያ የኢኮኖሚያዊ እና ፖለቲካዊ ጫና ለመፍጠር የተቃጡ የሳይበር ጥቃቶችን ማክሸፉን አስታውቋል። የሳይበር ጥቃት ሙከራው የተቃጣው ሳይበር ሆሩስ ግሩፕ (Cyber_Horus Group)፣ አኑቢስ ዶት ሃከር (AnuBis.Hacker) እና ሴኪዩሪቲ ባይ ፓስ (Security_By_Passed) በተባሉ የሳይበር አጥቂዎች አማካይነት መሆኑን ኤጀንሲው ገልጿል፡፡ ወንጀለኞቹ ለረጅም ጊዜ ሲዘጋጁ የቆዩ እና ኤጀንሲው ሲከታተላችው የነበሩ ሲሆን በይበልጥ አርብ ሰኔ 12/2012 እና ቅዳሜ ሰኔ 13/2012 ከፍተኛ የሚባል የሳይበር ጥቃት ሙከራዎች ማድረጋቸውን ገልጿል። በዚህ ጊዜ ዉስጥ የ13 የመንግስት፣ 4 መንግስታዊ ያልሆኑ ተቋማትን የድረ-ገጽን የማስተጓጎል ሙከራ ማድረጋቸውን አስታውቋል ኤጀንሲው አስታውቋል፡፡ የሳይበር ጥቃት ሙከራው በሀገሪቱ የመንግስት አገልግሎት ሰጪ ተቋማት፤ የደህንነት መስሪያ ቤቶች እና የግል ድርጅቶች ድረ-ገጽ ላይ ያነጣጠረ ነበር ተብሏል፡፡ ሳይበር ሆሩስ ግሩፕ፣ አኑቢስ ዶት ሃከር እና ሴኪዩሪቲ ባይ ፓስ የሳይበር ጥቃት አድራሽ ቡድኖች ሃላፊነቱን የወሰዱ ሲሆን ዋና አላማቸዉም ከህዳሴው ግድብ ዙሪያ በተለይ በውሃ አሞላል ጋር በተያያዘ ሁሉን አቀፍ ተጽእኖ በሀገሪቱ ላይ ለመፍጠር በማሰብ እንደፈጸሙት ተገልጿል፡፡ የሳይበር ጥቃት የተሰነዘረባቸው ተቋማት አብዛኛዎቹ በድረ-ገጽ ግንባታ ሂደት ደህንነታችው ታሳቢ ያላደረጉ ተቋማት፤ በቀጣይነት የደህንነት ፍተሻ ያላደረጉ እና ከፍተኛ የሳይበር ደህንነት ተጋላጭነት የነበረባቸው መሆኑን የኢንፎርሜሽን መረብ ደህንነት ኤጀንሲ አረጋግጧል፡፡ ኤጀንሲው አስቀድሞ ቅድመ ዝግጅት በማድረጉ ምክንያት እና ይህን መጠነ ሰፊ የሳይበር ጥቃት መከላከል ባይችል ኖሮ ጥቃቱ በሀገሪቱ ኢኮኖሚያዊ፤ ፖሊቲካዊ እና ስነ ልቦናዊ ጉዳት ሊያስከትል ይችል እንደነበር የገለጸው ኤጀንሲው በመከላከሉም ሊደርሱ የሚችሉ ከፍተኛ አደጋዎችን ማስወገድ መቻሉን እና ይህንንም ተግባር አጠናክሮ እንደሚቀጥልበት አሳውቋል፡፡ በቀጣይም መሰል ጥቃቶች በስፋት፤ በረቀቀ መንገድ እና ከተለያዩ ስፍራ ሊሰነዘር እንደሚችል ግምት ውስጥ በማስገባት ግለሰቦችም ሆኑ ተቋማት .et domain ከመጠቀማቸው በፊት የድረ-ገጻቸውን ደህንነት አረጋግጠው እንዲጠቀሙ፤ ራሳቸውን ከሳይበር ደህንነት ተጋላጭነት ለመከላከል እና አስፈላጊውን የጥንቃቄ እርምጃዎችን መውሰድ እንደሚኖርባቸው ኤጀንሲው አሳስቧል። ተቋማት ከኤጀንሲው ጋር በመተባበር ያለባቸውን የደህንነት ተጋላጭነት መድፈን እንዳለባችው እና የተለያዩ የሳይበር ደህንነት ጥቃት ሙከራ ሲያጋጥማቸውም ሆነ ሙያዊ ድጋፍ ሲያሻቸው ለኤጀንሲው በማሳወቅ አስፈላጊውን ትብብርና ድጋፍ ማግኘት እንደሚችሉ አስታወቋል። ባለፉት ሁለት ቀናት ትብብር ላደረጉልን ተቋማት እና ግለሰቦች በተለይ ለኢትዮ ቴሌኮምና ለኢኖቬሽን እና ቴክኖሎጂ ሚኒስቴር ኤጀንሲው ምሰጋና ማቅረቡን ከኤጀንሲው ያገኘነው መረጃ ይጠቁማል።
ኢዜማ

21/06/2020

Gebeya News 🗞📰

ዴክሳሜታሶንን በሚመለከት የተሰጠ ማሳሰቢያ!

(ዶክተር ሊያ ታደሰ - የጤና ሚኒስትር)

በቅርቡ የዴክሳሜታሶን (Dexamethasone) መድሃኒት ኦክሲጅን ወይም የመተንፈሻ መሳሪያ እገዛ ቢያስፈልጋቸው የኮቪድ-19 ህሙማን ዘንድ ሊከሰት የሚችለውን የሞት አደጋ መቀነስ እንዳስቻለ መገለፁ ይታወሳል።

ይህንንም ተከትሎ የጤና ሚኒስቴር በሀገራችን ኦክሲጅን ወይም መተንፈሻ መሳሪያ እገዛ ለሚያስፈልጋቸው የኮቪድ-19 ህሙማን የህክምና ባለሞያዎች በሚያዙት መሰረት ዴክሳሜታሶን እንደ ድንገተኛ ህክምና ጥቅም ላይ እንዲውል ተወስኗል።

ነገር ግን ዴክሳሜታሶን የኮቪድ-19 መድሃኒት ያለሆን እና ለመከላከል የማይጠቅም ሲሆን የራሱ የሆነ የጎንዮሽ ጉዳት እንዳለው ግንዛቤ እንዲወሰድ እና ያልታመሙ ሰዎች ያለ ህክምና ባለሙያ ትዕዛዝ ከወሰዱት ከጥቅሙ ይልቅ ጉዳቱ የሚያመዝን መሆኑ ሊታወቅ ይገባል።

ሕብረተሰቡ ያለ ሀኪም ትዕዛዝ መድሃኒቱን እንዳይወስድ እንዲሁም የፋርማሲ እና ሌሎች የጤና ባለሞያዎችም የዴክሳሜታሶን መድሃኒትን ያለ ሃኪም ትዕዛዝ ለደንበኞቻቸው መሸጥ እንደሌለባቸው በአፅንኦት እናሳስባለን።

21/06/2020

የፀሐይ ግርዶሽ እና ጥንቃቄ!

የፀሐይ ግርዶሽን በዓይን በቀጥታ መመልከት ቋሚ ጉዳት በዓይን ላይ ያደርሳል። ግርዶሹን ለመመልከት ፦

1. ደረጃውን የጠበቀ የግርዶሽ መነፅር መጠቀም

2. ፒን ሆል ካሜራ ወይም በአነስተኛ ቀዳዳ ወደ ድፍን ካርቶን የሚገባውን ብርሃን የሚስለውን ስእል ጀርባ ለፀሐይ በማዞር መመልከት

3. ጨለማ ክፍል ውስጥ በቀዳዳ የሚገባውን የፀሐይ ብርሃን መሬት ወይም ግድግዳ ላይ የሚሰራውን ስእል መመልከት

4. በዛፎች ቅጠል አልፎ መሬት ላይ የሚያርፈውን የፀሐይ ስእል መመልከት

5. ለቴሌስኮፕም ሆነ ባይነኩላር የፀሐይ ብርሃን መጣኝ ደረጃውን የጠበቀ ፊልተር ግጥሞ መመልከት

6. ግርዶሹን የሚያሳዩ የቀጥታ ስርጭቶችን መመልከት

የፀሐይ መነፅር ፣ ፍሎፒ ዲስክ ፣ የፎቶ ፊልም ፣የራጅ ፊልም እና የመሳሰሉት ቁሶች መጠቀም በዓይን ላይ ጉዳት ያደርሳል

Want your business to be the top-listed Clothing Store in Addis Ababa?
Click here to claim your Sponsored Listing.

Category

Telephone

Website

Address

Addis Ababa
00251