Walabu Source
The daily news, facts and information
17/12/2023
#ትዝብት1 walabusource
Gc Days
ከቅርብ አመታት ወዲህ በሀገራችን ዩኒቨርስቲዎች በተማሪዎች የተዘጋጁ የተለያዩ የአደባባይ ክብረ በአላትን መመልከት የተለመደ ሆናል።
እነዚህ ክብረ በአላት የተማሪዎችን የእርስ በእርስ ግንኙነት በማዳበር እንዲቀራረቡ እንዲፈላለጉ አንዳቸው የአንዳቸውን ባህል እና ማንነት እንዲረዱ እንዲያከብሩ እንዲያውቁ በማድረግ ከፍተኛ ሚና እየተጫወቱ ይገኛሉ ።
ሆኖም ግን አንዳንዴ ለክብረ በአላቱ የሚሰጡት ስያሜዎች በበአላቱ ላይ የሚከወኑ ሁነቶች ማለትም ዳንሶች ንግግሮች የተሳታፊዎች አለባበስ የበአሉ አስፈላጊነትና ጠቀሜታ ላይ ጥያቄ ማስነሳቱ አልቀረም ።
ትልቅ ሰው መሆን አይቀርም ወጣትነት: በጎልማስነት : ወንድነት :በአባትነት: ሴትነት: በእናት : መቀየሩ አይቀርምና ዛሬ ላይ ወጣትነት ነገሮችን ከማየት እና ከመሞከር ጉጉት ጋር ተቀላቅሎ ለቀልድም ሆነ ባለማወቅ የምናደርጋቸው ድርጊቶችና ፓስቶች ንግግሮች የነገው ህይወታችን አኗኗር እና ማንነታችን ላይ ተጽዕኖ ማሳደራቸው አይቀርምና እያስተዋልን ።
ትዝብት ቁጥር አንድ ከወላቡሶርስ
https://t.me/walabu_source
16/12/2023
Xiinxalaan siyaasaa Obbo johaar Mohammed waayee taayye dandayaafi mana keessaa baafamuu maatii isaatiin wal qabsiisee yaada toora media Hawaasaa isaarratti barreesseen Akkas jedhe "Siyaasa biyya keenyaa keessaa wanti fokkisaan tokko namoonni/ murnoonni gaafa waldhaban maatii walii kan miidhaniidha".
Itti dabaluunis Nuti warri qabsoo/siyaasa hojii godhannee filanne aarsaafi wareegama dhuunfaan dhufuu malu beekneeti itti seenne. Garuu ammoo haati, abbaan, adaadaan, haati warraa, obbolaanfi daa’imman keenya murtii kana keessatti hirmaannaa hin qaban. Badii uumamuufis wanti itti gaafatamaniif hin jiru. Taayyee Danda’aas tooraafi tooftaa siyaasaa filateen aarsaa itti dhufe kafalus, maatii isaa miidhuun garuu fafa. Yeroma mana itti kireeffatanis osoo hin kenniniif daa’imman isaa mana jireenyaa keessaa ari’uun cubbuudha.
Gochi akkanaa qaroowwan siyaasaa (political elites) jiddutti gadoo dhuunfaa hammeessuun, bor gaafa yeroon jijjiramte walitti fayyuu rakkisaa godha. Siyaasni haaloo ( revenge politics) ammoo biyya balleessa Jechuun Barreeffama isaa goolabeera.
https://t.me/walabu_source
https://vm.tiktok.com/ZM6MkfSpY/
https://youtube.com/?si=WMwrSWBruPoz550m
28/11/2023
ወይዘሮ ሮማነወርቅ ካሳሁን ከአባታቸው ከአቶ ካሣሁን እንግዳሸትና ከእናታቸው ከወይዘሮ አለሙሽ ዓለም በ1914 ዓ.ም አዲስ አበባ ከተማ ውስጥ ተወለዱ፡፡ እድሜያቸው ለትምህርት ሲደርስም ቅድሥት ሥላሴ ቤተክርስቲያን መንፈሳዊ ትምህርት ቤት ገብተው የቤተክርስቲያን ትምህርት ተማሩ፡፡ ከዚያም ስዊድን ሚሲዮን ትምህርት ቤት በመግባት በጊዜው ይሰጥ የነበረውን ዘመናዊ ትምህርት ተማሩ፡፡ በትምህርት ቤት ቆይታቸውም ጎበዝ ስለነበሩ አንደኛ ስለሚወጡ በአውሮፓውያን አስተማሪዎቻቸው ይሸለሙና ይመሰገኑ ነበር።
ወይዘሮ ሮማነወርቅ በተማሩበት ወቅት ሴቶች ላይ ከፍተኛ የባህል ተፅዕኖ ስለነበር ሮማነወርቅ ገና የ16 ዓመት ልጅ ሳሉ ለትዳር ታጩ፡፡ በለጋ እድሜያቸውም ወደ ትዳር ዓለም ተቀላቀሉና የአንዲት ሴት ልጅ እናት ለመሆን በቁ፡፡ በስዊድን ሚሲዮን ትምህርት ቤት ይማሩ በነበረበት ወቅት ከአውሮፓውያን መምህራን ያገኙት ዘመናዊ ትምህርት እንዲሁም ከተፈጥሮ ችሎታቸው ጋር ተደምሮ በጥናትና ንባብ ያዳበሩትን እውቀታቸውን ወደ አደባባይ ማውጣት ስለፈለጉ በጥር ወር 1939 ዓ.ም በወቅቱ የማስታወቂያና ፕሮፖጋንዳ ሚኒስቴር ተብሎ ይጠራ በነበረው መስሪያ ቤት የመጀመሪያዋ ሴት ጋዜጠኛ በመሆን ተቀጠሩ፡፡ ወይዘሮ ሮማነወርቅ የሴት ልጅ ስራ "ከማዕድ ቤት ነው" የሚለውን የወቅቱን የኅብረተሰቡን አመለካከት በመጋፈጥ በማስታወቂያ ሚኒስቴር ውስጥ በተሰጣቸው በሬዲዮ ጋዜጠኝነት ስራቸው የተለያዩ ጽሑፎችንና ዜናዎችን በማዘጋጀት በማራኪ አንደበታቸው ሲያንቆረቁሩት በዜና አቀራረባቸውና በፕሮግራም ዝግጅታቸው በሕዝብ ዘንድ ከፍተኛ ተወዳጅነትንና አድናቆትን ለማግኘት ብዙም ጊዜ አልወሰደባቸውም ነበር፡፡
በማስታወቂያ ሚኒስቴር ውስጥ ባገለገሉባቸው ጊዜያት በሬዲዮ ዜና አጠናቃሪነት፣ በዜና አንባቢነት፣ በሴቶች ፕሮግራም አዘጋጅነት ሰርተዋል፡፡ በዚሁ መስሪያ ቤት ውስጥ አንድም ቀን ሰለቸኝ ሳይሉ በየጊዜው ለአድማጭ አዲስ ነገር ይዞ በመቅረብ ለ25 ዓመታት ያህል ለሙያቸው በመታመን ያገለገሉት ጋዜጠኛ ሮማነወርቅ፣ ለሴቶች ብቻ ሳይሆን ለወንዶችም በተለይ ለጋዜጠኞች አርዓያ መሆን ችለዋል፡፡ ይህም ከፍተኛ የሆነ ተወዳጅነትንና አድናቆትን አስገኝቶላቸዋል፡፡
ወይዘሮ ሮማነወርቅ ካሣሁን የመጀመሪያዋ ሴት ጋዜጠኛ ብቻ አልነበሩም፡፡ ሴቶች ከወንዶች እኩል ተሰልፈው መስራትና ውጤት ማምጣት እንደሚችሉ ለኢትዮጵያውን ሴቶች ምሳሌና አርዓያ በመሆን ከቀዳሚዎቹ ተርታ የሚመደቡ ሰው ነበሩ፡፡ በትርፍ ጊዜያቸው ደግሞ በተለያዩ ማኅበራዊ ጉዳዮች ዙሪያ የሚያጠነጥኑ ጽሑፎችንም ያዘጋጁ ነበር፡፡ አብዛኞቹ ጽሑፎቻቸውም የሴቶችን ማኅበራዊ ኑሮ ማሻሻል ላይ ያተኮሩ ነበሩ፡፡
ወይዘሮ ሮማንወርቅ ካሣሁን የመጀመሪያ መጽሐፋቸውን (ትዳር በዘዴ) በ1942 ዓ.ም ለእትመት አብቅተዋል። ከአንድ ዓመት በኋላ በ1943 ዓ.ም ሁለተኛ መጽሐፋቸውን (ማህቶተ ጥበብ) ለሕትመት አበቁ፡፡ በ1948 ዓ.ም ሦስተኛ መጽሐፋቸውን ለሕትመት አበቁ፡፡ የመጽሐፉም ርዕስ "የሕይወት ጓደኛ" የሚል ነበር፡፡ ወይዘሮ ሮማነወርቅ የጤና እክል አጋጥሟቸው በሕክምና ሲረዱ ቆይተው ጥር 23 ቀን 1964 ዓ.ም አረፉ፡፡ ስርዓተ ቀብራቸውም በቀጨኔ መድኃኔዓለም ቤተ-ክርስቲያን ተፈጽሟል፡፡
28/11/2023
#ትግራይ
" የምንበላው አጥተናል ፤ የምንሄድበትም ጠፍቶን ጨልሞብናል። "
በባለፉት የክረምት ወራት ባጋጠመ የዝናብ እጥረት በተለያዩ #የትግራይ አካባቢዎች ከፍተኛ የድርቅ አደጋ መከሰቱን ተከትሎ ጉዳት እየደረሰ ነው።
በተለይ አበርገለ ጭላ ወረዳ የበረታ ድርቅ በመከሰቱ የሰዎች ህይወት እንዲጠፋ ምክንያት እንደሆነ በርካቶችም ከቄያቸው ወጥተው ወደልመና እንዲገቡ እንዳደረገ ተነግሯል።
አንዲት እናት ፦
" በየአካባቢያችን ድርቅ ስላጋጠመን ወደጭላና ሌሎች ቦታዎች ሄደን እየለመንን ነው።
በየአካባቢያችን ምንም እህል የለም። የተወስኑ አካባቢዎች ብቻ ነው የተወሰነ ዝናብ የዘነበው እንጂ አብዛኛው አካባቢ እህል የሚያበቅል በቂ ዝናብ አልዘነበም።
አብዛኛው ሰው ወደ ልመና ተሰማርቶ ነው ያለው።
እርዳታ እንኳን ከተቀበልን 1 ዓመት ሆኖናል ከዛ በኃላ ተሰጥቶን አያውቅም። አጠቃላይ የዚህ አካባቢ ማህበረሰብ ተጎድቷል። ሁሉም እየተቸገረ ስለሆነ አንዳንዴ ለምነንም አናገኝም። በርካታ ሰዎችም በረሃብ እየሞቱ ነው። መንግሥት እርዳታ ያድርግልን ልጆቻችንም ትምህርታቸውን ይቀጥሉ። "
አንዲት እናት
" ከልጆቼ ጋር በጣም ስለተራብኩ ነው ወደ ጭላ ከተማ የመጣሁት። እዚህም ምንም የለም። ልጆቼን ይዤ በጣም ተቸግሪያለሁ።
አምስት ልጆች አሉኝ ሲጨንቀኝ ጊዜ 3ቱን ልጆች ሰው ቤት አስጠግቼያቸዋለሁ። ሁለቱ ከእኔ ጋር ናቸው ግን የማበላቸው የለኝም። ከዚህም ከዚያም እየለመንን እየዋልን እያደርን ያለነው።
በጣም ከፍቶናል፤ እርዳታ ካቆመ ቆይቷል። አንዳንዴ ሲጨንቀኝ የቀን ስራ እየሰራሁ የልጆቼን እራት አገኝ ነበር አሁን ግን የቀን ስራም የለም የምንሄድበት ጠፍቶን ጨልሞብናል። "
አንዲት ልጅ ደግሞ ፦ በመራቧ ምክንያት ትምህርት ማቋረጧንና ወደ ጭላ የሚበላ ፍለጋ መምጣቷን ገልጻ ፤ በየቀኑ እየለመንን ነው የምንበላው ብላለች። እርዳታ ይሰጠን ስትል ተማፅናለች።
የድርቁ ተጎጂዎች አስከፊው ድርቅ እንዳለ ሆነ ለነፍስ ማቆያ የሚሆነው እርዳታ ተቋርጦ በመቆየቱ ህይወት ጨልሞብናል ፤ መንግሥት ህይወታችንን ይታደግ ብለዋል።
የወረዳው አስተዳደር ምን ይላል ?
የወረዳው አስተዳዳሪ አቶ ሃጎስ ሃደራ ፦
" ህብረተሰቡ በችግር ላይ ችግር ወድቆ አደጋ ላይ ነው ያለው። የክረምት ወቅቱ በጣም የዝናብ እጥረት ነበረበት ፣ተባይም እንዲሁ የማዳበሪያ አቅርቦቶም ችግር ነበር ሌሎችም ምክንያቶች ነበሩ እነዚህ ሁሉ ተደማምረው ህዝቡ ላይ የደረሰው አደጋ አስከፊ ነው።
ከ7 በላይ ትምህርት ቤቶች ተዘግተዋል። እስከ 5000 ሺህ የሚያህል ተማሪ ተበቷል። ተመዝግቦ ነበር አሁን የለም።
አስከፊ ረሃብ አለ፣ ሞትም አለ፤ እስካሁን ከ210 በላይ ሰዎች ህይወታቸው አልፏል፤ ከመድሃኒት እጥረት፣ ከምግብ እጥረት ጋር በተያያዘ ነው።
ችግሩን ለመፍታት የፌዴራል መንግሥት በማስተባበር ተግባራዊ ምላሽ ሊሰጥ ይገባል። የተፈናቀሉ ሰዎችም ወደ ቦታቸው እንዲመለሱ ማድረግ አለበት
መረጃው ነዋሪዎች እና የወረዳው አስተዳደር ለድምፂወያነ ቴሌቪዥን ከሰጡት ቃለመጠየቅ የተወሰደ ነው።
28/11/2023
#ከፖሊስ በተተኮሰ ጥይት አንዲት ወጣት ተገደለች
የ32 ዓመቷ ወጣት በፖሊስ ጥይት ከጀርባዋ ተመታ ህይወቷ ያለፈ ሲሆን ፖሊስ የድርጊቱ ፈፃሚ በቁጥጥር ስር ይገኛል ብሏል።
በአዲስ አበባ ከተማ ቂርቆስ ክፍለ ከተማ ወረዳ 11 ነዋሪ የሆነች የ32 አመት ወጣት ከፖሊስ አባል በተተኮሰ ጥይት ተመታ ህይወቷ አልፏል።
በፖሊስ አባል ጥቃት የደረሰባት ኢየሩሳሌም አስራት የቂርቆስ ክፍለ ከተማ ነዋሪ ስትሆን ጥቃቱ ካጋጠማት በኋላ በጥቁር አንበሳ ሆስፒታል የቀዶ ጥገና እና ሕክምና ክትትል ሲደረግላት የነበረ ቢሆንም ህይወቷ ሊተርፍ አልቻለም።
በቂርቆስ ክፍለ ከተማ ወረዳ 11 ቀበሌ 25 ህዳር 13 ቀን 2016 ዓ.ም ከምሽቱ 5 ሰአት አካባቢ በወጣቷ ጓደኞች እና በሌሎች ሰዎች መካከል በተፈጠረ አለመግባባት በቦታዉ የደረሰዉ የፖሊስ አባል በተተኮሰ ጥይት ህይወቷ እንዳለፈ ተገልጿል።
ጉዳዩን በተመለከተ የአዲስ አበባ ፖሊስ ኮሚሽን የህዝብ ግንኙነት ዳይሬክተር ምክትል ኮማንደር ማርቆስ ታደስ ፤ ወንጀሉን የፈፀመዉ የፖሊስ አባል በቁጥጥር ስር ዉሎ " ለምን እና በምን ሁኔታ ዉስጥ ሊተኩስ ቻለ ? " የሚለዉ ጉዳይ እየተጣራ ነው ብለዋል።
ወደፊትም እንደ አስፈላጊነቱ የፍርድ ሂደቱ በመከታተል ለህዝብ ይፋ እንደሚያደርግ አሳውቀዋል።
28/11/2023
የሙስናው መባባስ . . .
የህግ ባለሙያ አቶ ጥጋቡ ደሳለኝ ፦
" ሙሰኞች ላይ የሚወሰድ እርምጃ ጠንካራ ስላልሆነ ሙስና ከመቀነስ ይልቅ እንዲጨምር ሆኗል።
የፖለቲካ መዋቅሩ በራሱ አጥፊዎች እንዳይጠየቁ እድል የሚሰጥ ነው።
ሰዎች ሙስና ሰርተው ሲያጠፉ በግልፅ ማስረጃ ቀርቦባቸው ጥፋተኛ መሆን ሲገባቸው እንደውም ከለላና ሽፋን ሲያገኙ ፣ ከበሉበት ቦታ ወደሌላ ቦታ ዘወር ሲሉ ፣ ሃብትና ንብረት እንዲያገኙ ሲመቻችላቸው ይታያል።
ይሄ ሁሉ የፖለቲካ ስሪቱ ነው። የፖለቲካ ስሪቱ ብሄርን መሰረት ያደረገ መሆኑነው። ይሄ ብሄርን መሰረት ያደረገ አደረጃጀት በሙስና ላይ የሰላ ትግል እንዳይደረግና ተጠያቂነት እንዳይመጣ ያደርጋል።
የፖለቲካ ስርዓቱ #ብሄር እና #ትውውቅን መሰረት ያደረገ በመሆኑ በአጥፊውና በጠያቂው መካከል ልዩነት እንዳይኖር ሆኗል።
መፍትሄው ሙስና የሚፈፅሙ አጥፊዎችን ተጠያቂ ለማድረግ ህጉን ጠንካራ ማድረግ ብቻ ነው። "
28/11/2023
የመብቶች እና ዴሞክራሲ ዕድገት ማዕከል (ካርድ) ከሜታ ጋር በመተባበር ፈጠራ በተሞላበት መንገድ የሰላም መልዕክት አዘጋጅተው በማጋራት በርካታ ምላሽ ያገኙ የፌስቡክና ኢንስታግራም ተጠቃሚዎችን ለመሸለም ዝግጅቱን ማጠናቀቁ ይታወሳል።
ሆኖም ይህ ውድድር እስከ ታኅሣሥ 21 ድረስ ተራዝሟል። አሸናፊዎች ከ50 ሺሕ እስከ 100 ሺሕ ብር ድረስ ይሸለማሉ፡፡
በዚህ ውድድር ለመሳተፍ #ሰላምለኢትዮጵያእና ሃሽታጎችን ይጠቀሙ
27/11/2023
38 በመቶ አውሮፓዊያን በቀን ሶስቴ እንደማይመገቡ ተገለጸ
ከጠቅላላው የአውሮፓ ህዝብ ውስጥ 21 በመቶ በድህነት የሚኖር ነው ተብሏል
38 በመቶ አውሮፓዊያን በቀን ሶስቴ ምግብ የመብላት አቅም እንደሌላቸው ተገለጸ፡፡
742 ሚሊዮን የህዝብ ብዛት ያለው አውሮፓ 104 ትሪሊዮን ሀብት በመያዝ ከሁሉም አህጉራት ሀብታሙ አህጉር በመባል ይታወቃል፡፡
የአውሮፓ ባሮሜትር ይፋ ባደረገው ጥናት መሰረትም 38 በመቶ የአህጉሪቱ ህዝቦች በቀን ሶስት ጊዜ የመብላት አቅም እንደሌላቸው ገልጿል፡፡
በሁሉም የህብረቱ አባል ሀገራት ካሉ 10 ሺህ ዜጎች በዚህ ጥናት ላይ ተሳትፈዋል የተባለ ሲሆን በጥናቱ ከተሳተፉት ውስጥ 15 በመቶዎቹ ብቻ የኑሮ ውድነት እና የምግብ ዋጋ መናር አያሳስበንም ብለዋል ሲል ሮይተርስ ዘግቧል፡፡
እንደ ዘገባው ከሆነ በየዓመቱ እየናረ የመጣው የነዳጅ እና ምግብ ዋጋ ህይወታቸውን እየፈተነው ነው ያሉ ሲሆን በተለይም ችግሩ እየሰፋ የመጣው ባለፉት ሶስት ዓመታት ውስጥ ነው፡፡
በጥናቱ መሰረትም 29 በመቶ አውሮፓዊያን የገንዘብ አቅማቸው አደጋ ውስጥ ወድቋል የተባለ ሲሆን ከሁለቱ አውሮፓዊያን አንዱ በቀጣዮቹ ወራት ውስጥ ወደ ገንዘብ ቀውስ የመግባት አደጋ አንዣቦባቸዋልም ተብሏል፡፡
ከዚህ በፊት በተደረገ ጥናት 17 በመቶ አውሮፓዊያን የድህነት አደጋ ውስጥ ሲሆኑ ከ75 በመቶ በላይ አውሮፓዊያን ደግሞ በዋጋ መናር ምክንያት የገንዘብ አጠቃቀማቸውን ለማመጣጠን መገደዳቸውን ተናግረዋል፡፡
የአውሮፓ ህብረት በኢትዮጵያ ያለው የሰብዓዊ መብት ጥሰት አሳስበኛል አለ
በብሪታንያ 6 ሚሊዮን ገደማ ዜጎች ዝቅተኛ ገቢ አላቸው የተባለ ሲሆን ምግብ እና መሰል መሰረታዊ ፍላጎቶቻቸውን ማሟላት እማይችሉበት ደረጃ ላይ እንደሆኑ ተገልጿል፡፡
እነዚህ በድህነት ውስጥ የሚኖሩ አውሮፓዊያን የምግብ ፍላጎቶቻቸውን ለመሸፈን ቅናሽ ያላቸው የምግብ ባንክ እና ሌሎች ማህበራትን እየፈለጉ ነውም ተብሏል፡፡
በአጠቃላይ በኑሮ ውድነቱ ምክንያት በቀን ሶስቴ እየተመገቡ ያሉት 42 በመቶ የአህጉሪቱ ነዋሪዎች ብቻ ናቸው የተባለ ሲሆን 21 በመቶዎቹ ደግሞ ልጆቻቸውን ለመመገብ ሲሉ ቢያንስ አንድ ጊዜ የግድ መመገብ እንደሚያቆሙ በጥናቱ ላይ ተጠቅሷል፡፡
ለተጨማሪ ፈጣን እና እውነተኛ መረጃዎች 👇👇👇👇
27/11/2023
26/11/2023
#የአርሰናሉ አሰልጣኝ ማክል አርቴታ ባለፉት 20 ዓመታት #አርሰናልን ካሰለጠኑ አሰልጣኞች በላይ ጨዋታዎችን በማሸነፍ ቀዳሚ መሆን ችሏል
Mikel Arteta has more wins than any other manager in their first 200 matches 👏
Click here to claim your Sponsored Listing.
30/11/2023
27/11/2023