Abu Raslan Mujahid

Abu Raslan Mujahid

Share

Conflict is almost an inherent part of human nature which dates back to the early history

Photos from Natnael Mekonnen's post 10/08/2025
06/10/2024

"As Finfinneetti miti kirkirri lafaa kan uumame. Dambalichi lafa jalaa imalee as ga’e malee kirkirri kan mudate Awaash*tti yommuu ta’u Rekter Iskeeliidhaa 4.9 ta’a" - Dr. Eliyaas Leewii

Yuunivarsiitii Finfinneetti Daarektarri Ji'oo Fiiziksii fi Saayinsii Hawaa Doktar Eliyaas Leewii Televijiinii biyyalessaaf ibsa kennaniin

"Akka odeeffannoo hanga ammaatti argameen kirkirri lafaa kun kan mudate as Finfinneetti osoo hin taane, Awaash*tti.

Garuu lafa jala deemee as Finfinneefi bakka adda addaatti dhagahamee gamoo raase.

Iskeelii Riiktarii 4.9 kan ta’u kirkirri Awaash*tti mudate kun gaara Fantallee jedhamurraa hanga naannoo Matahataatti kan dheeratudha.Odeeffannoon hanga ammaa jiru kana fakkaata.

Ummanni tasgabbaa'uu qaba. Sirriidha, dhaga'amuu danda'a garuu dhiheenyatti miti

Odeeffannoo dabalataa akkuma arganneen isin beeksifna. “ Jedhan.

Kirkirri lafaa kun Itoophiyaa bakkoota garaa garaatti dhaga’amaa akka jiru jiraattoonni miidiyaa
tti himaa jiru.

06/10/2024

Aadaan keenya Amantaa keenyadha
ባህላችን ሃይማኖታችን ነዉ።

01/10/2024
17/08/2024

2,000,000 ብር ለሱ ስድብ ከሆነ የነ ደሞዝ እሪግማን ነው ልበል

08/01/2024

እክዋኑል ሙስሊሞች እሄን የሼክ ኢሊያስ አህመድን ዳዋ በደምብ እያሰራጩ ነዉ ።
ምን ተገኘ?

28/04/2021

ተከታታይ ትምህርቶች ስለረመዳን

ክፍል 01 ፆም ምንድን ነው ? የፆም ጥቅም እና የፆም ህግጋቶች

የሰው ልጅ ያለ መመሪያና ደንብ ልጓም እንደሌለው ፈረስ በመሆኑ በየትኛውም የህይወት ዘርፍ የሰው ልጅ መመሪያ ያስፈልገዋል። ሆኖም ፆመኛ ሙስሊም እንደሌሎቹ የእምነቱ ስርአት ሊከተላቸውና ሊተገብራቸው የሚገቡ መመሪያና ደንቦች እንደሚከተለው ተብራርተዋል።

የፆመኛ ሙስሊም መመሪያ በአሏህ ስም እጅግ በጣም ርህሩህ እጅግ በጣም አዛኝ በሆነው። በሸኽ ሙሐመድ ቢን ሷልህ አል-ኡሰይሚን ትርጉም በአህመድ የሱፍ

ምስጋና ለአለማት ጌታ ለአሏህ ይገባው። የአሏህ ሰላምና እዝነት የነብያቶች መደምደሚያ በሆኑት በነብዩ ሙሐመድ(ሰ.ዐ.ወ)፣ በቤተሰቦቻቸውና በሶሃቦቻቸው ላይ ይሁን። ማንኛውም ሙስሊም ሊያውቃቸው የሚገቡ ጠቃሚ የፆም ህግጋቶች እንደሚከተለው ቀርበዋል።

ፆም ምንድነው?

ሲያም (ፆም) ከንጋት ጀምሮ ፀሐይ እስከምትጠልቅበት ጊዜ ድረስ ከምግብ ፣ ከመጠጥ እና ከግብረስጋ ግኑኝነት እንዲሁም ከሃራም ነገሮች ሁሉ በመቆጠብ አሏህን መገዛት ነው።


يَا أَيُّهَا الَّذِينَ آمَنُوا كُتِبَ عَلَيْكُمُ الصِّيَامُ كَمَا كُتِبَ عَلَى الَّذِينَ مِن قَبْلِكُمْ لَعَلَّكُمْ تَتَّقُونَ

እናንተ ያመናችሁ ሆይ ጾም በነዚያ ከናንተ በፊት በነበሩት (ሕዝቦች) ላይ እንደ ተጻፈ በናንተም ላይ ተጻፈ (ተደነባ) ልትጠነቀቁ ይከጀላልና፡፡

أَيَّامًا مَّعْدُودَاتٍ ۚ فَمَن كَانَ مِنكُم مَّرِيضًا أَوْ عَلَىٰ سَفَرٍ فَعِدَّةٌ مِّنْ أَيَّامٍ أُخَرَ ۚ وَعَلَى الَّذِينَ يُطِيقُونَهُ فِدْيَةٌ طَعَامُ مِسْكِينٍ ۖ فَمَن تَطَوَّعَ خَيْرًا فَهُوَ خَيْرٌ لَّهُ ۚ وَأَن تَصُومُوا خَيْرٌ لَّكُمْ ۖ إِن كُنتُمْ تَعْلَمُونَ

የተቆጠሩን ቀኖች (ጹሙ)፡፡ ከእናንተም ውሰጥ በሽተኛ ወይም በጉዞ ላይ የኾነ ሰው ከሌሎች ቀኖች ቁጥሮችን መጾም አለበት፡፡ በእነዚያም ጾምን በማይችሉት ላይ ቤዛ ድኻን ማብላት አለባቸው፡፡ (ቤዛን በመጨመር) መልካምንም ሥራ የፈቀደ ሰው እርሱ (ፈቅዶ መጨመሩ) ለርሱ በላጭ ነው፡፡ መጾማችሁም ለናንተ የበለጠ ነው፤ የምታውቁ ብትኾኑ (ትመርጡታላችሁ)፡፡

شَهْرُ رَمَضَانَ الَّذِي أُنزِلَ فِيهِ الْقُرْآنُ هُدًى لِّلنَّاسِ وَبَيِّنَاتٍ مِّنَ الْهُدَىٰ وَالْفُرْقَانِ ۚ فَمَن شَهِدَ مِنكُمُ الشَّهْرَ فَلْيَصُمْهُ ۖ وَمَن كَانَ مَرِيضًا أَوْ عَلَىٰ سَفَرٍ فَعِدَّةٌ مِّنْ أَيَّامٍ أُخَرَ ۗ يُرِيدُ اللَّهُ بِكُمُ الْيُسْرَ وَلَا يُرِيدُ بِكُمُ الْعُسْرَ وَلِتُكْمِلُوا الْعِدَّةَ وَلِتُكَبِّرُوا اللَّهَ عَلَىٰ مَا هَدَاكُمْ وَلَعَلَّكُمْ تَشْكُرُونَ

(እንድትጾሙ የተጻፈባችሁ) ያ በርሱ ውስጥ ለሰዎች መሪ ከቅን መንገድና (እውነትን ከውሸት) ከሚለዩም ገላጮች (አንቀጾች) ሲኾን ቁርኣን የተወረደበት የረመዳን ወር ነው፡፡ ከእናንተም ወሩን ያገኘ ሰው ይጹመው፡፡ በሽተኛ ወይም በጉዞ ላይ የኾነም ሰው ከሌሎች ቀኖች ቁጥሮችን (በልኩ) መጾም አለበት፡፡ አላህ በእናንተ ገሩን (ነገር) ይሻል፡፡ በእናንተም ችግሩን አይሻም፡፡ ቁጥሮች

27/04/2021

ሃይማኖትን ለምርጫ ፍጆታ ማዋል
~~~~~~~~~~~~~
በ1997 ምርጫ ጊዜ ግንባር ቀደሙ የኢህአዴግ ተገዳዳሪ ፓርቲ የነበረው ቅንጅት ነገሮች አልጋ ባልጋ ሳይሆኑለት ቀሩ እንጂ ለኢስላምና ለሙስሊሞች ግልፅ ስጋት ነበር። በጊዜው ከቅንጅት ከፍተኛ አመራሮች አንዱ የነበረው ብርሃኑ ነጋ ያለምንም ሃፍረት የፈረንሳዩን ፀረ–ሒጃብ ህግ እንደሚደግፍ በግልፅ ነበር የተናገረው። ከሙስሊሞች በኩል ፓርቲው "ፀረ–ኢስላም ነው" የሚለው ጩኸት ሲያይል ጊዜ የያኔው ሰለፊያ ጋዜጣ ላይ ቀርቦ ‘እኔ ማለት የፈለግኩት ልጆቻችን ተወያይተው፣ ተስማምተው ያስቀሩታል ማለቴ እንጂ እኛ እናግዳለን ማለቴ አይደለም’ ብሎ ነበር። (ቃል በቃል አይደለም።) በውጭ ጉዳይ ፖሊሲ ላይ ክርክር ሲደረግም ‘ኢትዮጵያ ከኬንያና ደቡብ ሱዳን በስተቀር በዐረብ ሃገራት ስለተከበበች ስጋት ተደቅኖባታል’ የሚል የደርግን ያረጀ ያፈጀ "የኢትዮጵያ ታሪካዊ ጠላቶች" ትርክት አስተጋባ። ፖለቲከኛ በተለይ በምርጫ ቅስቀሳ ወቅት መራጮቹን ከሚያስከፋ ቃል ይጠነቀቃል። እንዲያውም ሃሰተኛ የተስፋ ቃል እየገባ ሊያማልል ይሞክራል። ከብርሃኑ ነጋ የታየው ግን ከዚህ ተቃራኒ ነበር። ሰውየው ወይ የፖለቲካ ብስለቱ ለእድሜውና ለአካደሚ ማእረጉ የሚመጥን አይደለም። ወይ ደግሞ ለኢስላምና ለሙስሊሞች ያለው ጥላቻ ከፖለቲካ ትርፉ በልጦበታል። አለያ ደግሞ በፀረ ኢስላም አቋሙ ለኢስላም ጥላቻ ያላቸው ምቀኞችን ድምፅ ማግበስበስ ፈልጓል። ከዚህ ሊወጣ አይችልም።
ዛሬ በኔ ላይ የሚያሴር አካል "አያቴ ሙስሊም ነበረች" እያለ ሊደልለኝ አጉል ይሟሟታል። አሄሄ! "ውሻ ጭራውን የሚቆላው ላንተ ሳይሆን እጅህ ላይ ላለው ዳቦ ነው።" ገና ስልጣን ሳይዝ እንዲህ አይነት እኩይ አላማውን ግልፅ ያወጣ ሰው ኩርሲዋን ቢቆናጠጥ ምን ሊያደርግ እንደሚችል መገመት ነው እንግዲህ።
ልደቱ አያሌውም "የኢትዮጵያ ህዝብ’ኮ የዘውድ ስርአትን ሲናፍቀው ነው የሄደበት" እንዳለ ሲወራ ሰምቻለሁ። በራሴ ግን አላረጋገጥኩም።
በጊዜው በቅንጅት ደጋፊዎች ኢህአዴግ የሙስሊም አክራሪነትን እንዳስፋፋ፣ በሃገሪቱ ከኢህአዴግ መምጣት ጀምሮ የሙስሊሞች ቁጥር በከፍተኛ መጠን እንደጨመረ እና መሰል ይዘት ያላቸው ፅሁፎች ለምእራባውያን ጭምር እንደተፃፉ በሰፊው ሲሰራጭ ነበር።
ከመሆኑም ጋር ብዙ ህዝብ በኢህአዴግ ክፉኛ ተንገሽግሾ ስለነበር ለነዚህ ጉዳዮች ተገቢ ትኩረት አልሰጠም ነበር። ብርሃኑ ያንን ክፉ ንግግሩን በተናገረበት መድረክ ላይ ባቀረበው ኢኮኖሚ–ተኮር ሪፎርም (በተለይም ግብር ጋር በተያያዘ) ተሸንግለው "ለምን መርካቶ ቢሮ አትከፍቱም?" ያሉ ነጋዴዎች ነበሩ። (እርግጥ ነው "እምነታችንን በሆዳችን አንለውጥም" ብለው መድረክ ረግጠው የወጡ ቆፍጣናዎች እንደነበሩም ሰምቻለሁ።)
በሌላ ጫፍ ኢህአዴግም ሃይማኖትን ለምርጫ ፍጆታ የመጠቀም ዝንባሌ እንደነበረው በተጨባጭ የሚስተዋል ነበር። ቅንጅትን ጎጃም ላይ ፀረ ክርስትና፣ ወሎ ላይ ፀረ ኢስላም አድርገው በማቅረብ ህዝብ ሲቀሰቅሱ እንደነበር ሰምቻለሁ። በራሴም የታዘብኳቸው ነገሮች ነበሩ። ዱዓትና መሻይኾች ጭምር የኢህአዴግ አባላት ሆነው፣ የኢህአዴግ የምርጫ ምልክት (ንብ) ያለበት ቲሸርት ለብሰው ሲቀሰቅሱ እንደነበር የሚታወስ ነው።
ከምርጫ በሁዋላ ምን ተከሰተ? ለብዙዎች እንደማይሰወረው ቅንጅት ውጥንቅጡ ወጣ። ኢህአዴግ ደግሞ ከወትሮው በተለየ መልኩ በኢስላም ላይ ዘመተ። አሕባሽን ከትቢያ አንስቶ በግላጭ አዝሎ በመዞር ሙስሊሞች ላይ ታይቶ ተሰምቶ የማይታወቅ ውርጅብኝ አወረደ። በአይናችን የምናየውን ገልብጦ በፕሮፓጋንዳ ማሽኖቹ አጉል ሊግተን ተጋጋጠ።
ዛሬም ተመሳሳይ ድባብ ላይ ያለን እየመሰለኝ ነው። ሙስሊሞ

Want your practice to be the top-listed Law Practice in Addis Ababa?
Click here to claim your Sponsored Listing.

Category

Telephone

Address

Addis Ababa
132