Fedralist Unity

Fedralist Unity

Share

follow to get new updates news jokes & any polotical analyses

Mujib Amino Z islam 06/07/2022

እናም የረሱልን አደራ ችላ ያልን በሚመስል መልኩ ሶላትን ዘንግተናል። የረሱል አደራ ምን ነበር? ይህን ሁላችሁም የምታዉቁትን ታሪኽ ላጋራችሁ፦

በነብዩ (ሰዐወ) ላይ ሕመም ይጠናባቸው ጀመር። ዓኢሻ (ረዐ) ቤት ሆነው ታስታምማቸው ዘንድ እንዲፈቅዱላቸው ሚስቶቻቸውን ሁሉ አስፈቀዱ። ፈቀዱላቸውም።

የመጨረሻዎቹ ሰዐታት ሲደርሱ ሶሀቦች ሁሉ በነብዩ(ሰዐወ) መስጂድ ተሰባስበው ክፍ ባለ ድምፅ ያጉረመርሙ ጀመር።ረሱል(ሰዐወ) ድምፅቸውን ሰምተው ምን እንደሆኑ ሲጠይቁ። በርሳቸው ተረብሸው እንደሆነ ተነገራቸው።

ረሱልም (ሰዐወ) “ተሽክማቹ ያሉበት ውሰዱኝ” አሉ። እንደደረሱም ሶሀቦች እንዲህ አሏቸው “እናተ ሰዎች ሆይ! የኔ ሁኔታ አስፈርቷችኃልን?? ሶሀቦችም “አዎን አንቱ የአላህ መልዕክተኛ” በማለት መለሱላቸው እርሳቸውም እንደሚከተለው አሏቸው። “እናንተ ሰዎች ሆይ! የእኔና የእናንተ የቀጠሮ ቦታ ዱኒያ አይደለችም።ቀጠሮችን ሀውድ ዘንድ ነው።ከዚሁ ሆኜ ያየሁት ይመስለኛል።እናተ ሰዎች ሆይ የሶላት ነገርን አደራ፦ አሏህን ፈርታቹ ሴቶቻችሁን ጠብቁ። እናንተ ሰዎች ሆይ! ድህነት ያገናችኃል ብዬ አልፈራም።ይልቁንም በኃብት ትጥለቀለቁና ስትፎካከሩ ያለፉት ህዝቦች እንደጠፉት ሁሉ እናንተም ሀብት ያጠፋችኃል ብዬ እፈራላችኃለው።”

“እነንተ ሰዎች ሆይ! አላህ ባሪያውን ከዚህ አለምና እርሱ ጋር ከመገናኘት የትኛውን እንደሚመርጥ አማረጠው።ባሪያውም በአሏህህ ጋር መገናኘትን መረጠ።” ሶሀቦች ንግግራቸውን ጸጥ ረጭ ብለው ያዳምጡ ነበር።•••

ይልቅስ የገበያና የአውራ ጎዳናዎች፣ የመጓጓዣና የንግድ ማዕከላት ጭርታ ሳይሆን አስፈሪው ጭርታ የመስጂድ ጭርታ ነው። ምን ነበር የረሱል የመጨረሻ ቃል?
«ሶላታችሁን አደራ!!!»


▬▬▬▬▬▬▬▬▬
የቴሌግራም ቻናል-

Mujib Amino Z islam You can view and join right away.

06/07/2022

አስፈሪው ጭርታ
▬▬▬▬▬▬▬▬▬●●▬▬▬▬▬▬▬▬▬

©Mujib Amino

ሰዎች የሚርመሰመሱባቸው አውራ ጎዳናዎች፣ ብዙዎች የሚበዙባቸው የንግድ ስፍራዎች፤ የግብይት ና የአገልግሎት ተቋማት ሕንጻዎች፣ ባንኮች፤ የመጓጓዣ ተራዎች፣...ወዘተረፈ በጭርታ ዝምታቸው ያስተጋባል።

ከተማው ኦና ሆኗል። ሕዝብ ቅሬታ ውስጥ ያለ ይመስላል። መንግስት እየፈጸመ ያለዉን አሰራርና ሕግጋት እንዲያስተካክል መጠቆሚያ አንዱ ማሳያም ይሆናል።

ዜጎችን ጠብቅ ተንከባከብ፣ የኑሮ ዉድነቱን አረጋጋ፣ ሕገ መንግስቱን አክብር አስከብር፤ አብሮነትና አንድነትን ስበክ፣ ዲሞክራሲያዊ መብቶችን አትጣስ፣ የፕሬስ ነጸነት ይረጋገጥ፤•••የሚሉ ሐሳቦችን እያዉጠነጠኑ ማህበረሰሰቡ ፣ ወጣቱና ፖለቲለኛዉ •••የተቃዉሙን ሐሳብ ከአደባባይ ይልቅ በየቤቱ ተቅምጡ በጭርታ ድምጹን ለማሰማት እየጣረ ነው።•••

ጭርታዉ••• ከነፍስ መገንቢያ፤ ከልብ ማጽጃና ማጎልበቻ፤ ከአካል ብርታት ፤ ከሞራል ከፍታ፤ ከስነ ምግባር ማስዋቢያ፤ ከኢማን ማዕድ፣ ከፍቅር ገበታ፣ ከፍቅር አክሊል፤ ከውዴታ ማሳ፣ ከክብር ምንጭ፣ ••• የጌታችን ቀጥተኛ ትእዛዝ በውዱ ነብይ የተላከልን ውዱን ስጦታ በጭርታ አመጽነው።

በአቅራቢያዬ የሚገኝ መስጂድ ለፈጅር ሶላት አመራሁ። በመስጂዱ ውስጥ እንደገባሁ፤ ኢማማችን ነቢያዊ ፈለግ ተከትሎ፣ ምዕመናኑ ረድፉን ያስተከክል ዘንድ ወደቀጭ ወደግራ እያየ «ኢስተዉ፣ ወተራሱ፣ ወሱዱል ኸለል ... ተስተካከሉ፣ ክፍተት ዝጉ፣ ...ተጠጋጉ፣ ተቀራረቡ•••»

ኢማማችን በምዕመናን ጭርታ መስጂዱ ኦና በመሆኑ ምን ያህል ይሰማዉ ይሆን? ምን ያህል ይሸማቀቅ ይሆን? በሰጋጆች የሚሞሉት ረድፎች በጭርታ ተተክተዉ መመልከት ምነኛ ያማል?... 1 ሶፍ መሙላት ተሳነን•••

ጭርታዉ••• ከዚህ ሁሉ ዉለታና እዝነት ቡኃላ አሏህ ላይ ቅሬታ ለማቅረብ ነው? ጭርታዉ••• የሰጠንን ሲሳይ ለማስተባበል ነው? ጭርታዉ•••አሏህን ለማመጽ የተሰናዳ ነው? ጭርታዉ•••የሸይጧን ምርኮኛነትን ለማወጅ ነው?ጭርታዉ••• ተዝቆ የማያልቀዉን ውለታውን ለማሳነስ ነው?፤ ጭርታዉ•••ሪዝቅ አነሰብን ነው?፣ ጭርታዉ•••ምቾት አሽቆለቆለብን ነው?፣ ጭርታዉ •••ሀብትና ንብረት ወደመብን ነው?፣ ጭርታዉ •••አሏህ ላይ ተጽዕኖ ለማሳደር ነው? •••እ ? ? ?

ማሰብ የሚችል አእምሮ፣ መስማት የሚችል ጆሮ፣ መመልከት የሚችል ዓይን፣ መናገር የሚችል አንደበት፣ መንቀሳቀስ የሚችል እግር፣ መያዝና መጨበጥ፡ መስጠትና መለገስ የሚችል እጅ የሰጠን እሱ አይደለምን? (ሱረቱ-ነሕል 78)፡፡

“የአሏህንም ጸጋ ብትቆጥሩ አትዘልቋትም፤ አሏህ በእርግጥም መሐሪ አዛኝ ነውና።” (ሱረቱ-ነሕል 18)፡፡

በዚህ አንቀጽ ብቻ እንኳ እኛ የጌታችን አሏህ የውለታው ባለ-ዕዳዎች መሆናችንን መረዳት ይቻላል፡፡ አሏህ ለውለታው ክፍያን ቢጠይቀን ኖሮ ምን ይሆን መልሳችን? ለዚህ ውለታ የተጠየቅነው ክፍያ “ምስጋና” ብቻ ነው፡፡

ደግሞም የምናመሰግነውም በጸጋ ላይ ሌላ ጸጋ ሊጨመርልን እንጂ ጌታችን የምስጋና እጥረት ኖሮበት አይደለም፡-
“ጌታችሁም፦ ብታመሰግኑ በእርግጥ እጨምርላችኋለሁ ብትክዱም (እቀጣችኋላሁ)፤ ቅጣቴ በእርግጥ ብርቱ ነውና በማለት ባስታወቀ ጊዜ (አስታውሱ)።” (ሱረቱ ኢብራሂም 7)፡፡
አላህን ከማመን ብናፈገፍግ እራሳችንን እንጎዳለን እንጂ እሱን አንጎዳውም፡፡ እሱ ከፈለገ የሚወዳቸውንና የሚወዱትን መልካም ባሮች መፍጠር ይችላል።

05/07/2022

በድጋሚ ሙስሊም ወሎዬዎች ተጨፈጨፉ
===========================

Majlisa Oromiyaa - የኦሮሚያ መጅሊስ - Oromia Mejlis

በቄለም ወለጋ ዞን በመቻራ ወረዳ መንደር 20 ቀበሌ ውስጥ በወሎ ሙስሊሞች ላይ አሰቃቂ ጭፍጨፋ ተፈፅሟል። 😭😭😭 ኢናሊላሂ ወእና ኢሌይሂ ራጂኡን። ቁስለኞች ሆስፒታል አጨናንቀዋል። የሟቾች ቁጥር ብዙ መሆኑን የደረሰን መረጃ ያመልክታል። ከማህበረሰቡ የደረሰን መረጃ በኦነግ የታጣቂዎች እንደተፈፀመ አሳውቀውናል። ታጣቂዎቹ በቅርብ ግዜ በምዕራብ ወለጋ ቶሌ ወረዳ በመቶዎች የሚቆጠሩ ሙስሊሞች ተጨፍጭፈዋል። ተፈናቅለው ያሉትም አስፈላጊ እርዳታ አልደረሳቸውም። 😭😭😭😭 የወሎዬዎች ሞት መች ያበቃ ይሆን❓ ሃላፊነቱስ ማን ይወስዳል❓
ለፖለቲካ ፍጆታ ለምን የሙስሊሞች ደም ይፈሳል❓ እስከመቼ❓
የኦሮሚያ መጅሊስ ድርጊቱን አጥብቆ ያወግዛል። ሀገርን እያስተዳደረ ያለው መንግስት ነው። ስለዚህ ይህንን ጉዳይ በአስቸኳይ አጣርቶ የማያዳግም እርምጃ እንዲወስድ አጥብቀን እንጠይቃለን። የቶሌ ጉዳይ ፈር ሳያገኝ በድጋሚ መከሰቱ አሳፋሪ ነው።
የአላህ ወንድሞቻችን የሸሂድነት ደራጃ የቆሰለቱን ፈውስን ለቤተሰባቸው ሰብርን ወፍቃቸው። አሚን

05/07/2022

ሽፋኑ «አማራ» በሚል ይሁን «ሙስሊሞች» ላለፉት ዓመታት በጅምላ ሲጨፈጨፊ እንደነበረው ሁሉ የወሎ ሙስሊሞች በዚሁ በሰኔ ወር እንኳ ለሁለተኛ ጊዜ ዛሬ ደግሞ በተመሳሳይ መንገድ በቄለም ወለጋ በኦነግ ሸኔ በጅምላ እንደተገደሉ ሰማን።እጅግ የሚያሳዝንና የሚወገዝ እኩይ ተግባር!

ሰላማዊ ዜጎችን በማንነታቸው ኢላማ አድርጎ ግድያ ሲፈጸም ጉዳዩ ግድያ ብቻ አይሆንም። ኢሰብኣዊነትና በሰው ህይወት ቁማር መጫወት ነው! ጀግና ነኝ ያለ ኃይሉን መሳሪያ ባልታጠቁ ንጹኻን ላይ ሳይሆን ከታጠቀ ወታደር ጋር ይግጠምና ያሳይ!

ላለፉት ዓመታት በተደጋጋሚ ንጹኋን ሲጨፈጨፉ በተመሳሳይ መንገድ ጮህን፣አወገዝን።«እርምጃ እየተወሰደ ነው» ተባለ።ከፖለቲካ ሸፍጥ በራቀ ሁኔታ መፍትሄው ላይ በማተኮር የእውነት ከልብ መነጋገር ባለመቻሉ ንጹኻንን መታደግ አልተቻለም!

በተመሳሳይ መንገድ የንጹኻን ጭፍጨፋ ለስንተኛ ጊዜ መሆኑ ነው? አሁንም እንደከዚህ ቀደሙ በዚያው መንገድ ቀጣዩ ግድያ እስኪፈጸምና ይህኛውን እስኪያስረሳ ድረስ የዛሬውን ግድያ በማውገዝና በመጮህ ብቻ መፍትሄ ይመጣ ይሆን? ባለፉት ዓመታት ከተጓዝንበት በተለየ መንገድና ዓይን ጉዳዩን ለመረዳት ሞክረን የተለየ መፍትሄ ካልፈለግን በሀገራችን የንጹኻን ዜጎች እንዳይቀጥል ያሰጋል! ሁሉን የምታውቀው አምላኬ ሆይ! ሰላምና ምህረትህን! '
© Ahmedin Jebal

15/10/2021

Meski Menge Challenge Accepted
Pic :- በወለጋና ቦረና ሂወታቸውን ላጡ ወገኖች
Ani gaheekoo niin bahadhaa isinoo?
Hamma fi Suuraa kanaaf kennitaniin qarshii Lama Lama (2, 2)
Just for 24 hours

እኔ ሀላፊነቴን እወጣለሁ፣ እናንተስ?
ቦረና ላይ በደረሰ ድርቅ ምክንያት አርብቶ አደር የሆነው የቦረና ማህበረሰብ፣ የሚያረባው እንሰሳው በርሃብ፣ ብውሃ ጥም ከብቶቹ እያለቁበት ይገኛል። እስካሁን በታየ Data መሰረት ከ 4500 በላይ እንሰሳቶች ሞተውበታል።

ይህንን ምክንያት በማድረግ ፣ ንብረቱ እየወደመበት ላለው ማህበረሰብ፣ የእንስሳት መኖ እና ውሃ ለማድረስ ይሆን ዘንድ account ተከፍቶ ገንዘብ መዋጮ ማድረግን ጀምረናል።

እኔም እንደ አንድ ዜጋ ይህን ፎቶ ቻሌንጅን በመጠቀም በዚህ ፎቶ ለሚገኘው like፣ comment እና share ለያንዳንዱ 2 ብር ለመክፈል ወስኛለሁ።

14/10/2021

fghjertyjty 660

Photos from Fedralist Unity's post 29/06/2021

Qaalii oromo

10/05/2021
Want your business to be the top-listed Media Company in Addis Ababa?
Click here to claim your Sponsored Listing.

Website

Address

Addis Ababa
401