Go Singer Efi
Contact information, map and directions, contact form, opening hours, services, ratings, photos, videos and announcements from Go Singer Efi, Singer, http://www. fb. com/gosingerefi. com, Addis Ababa.
14/06/2026
# #ዳንኤልም መልካም መንፈስ ስላለው ከአለቆችና ከመሳፍንት በለጠ ፤ ንጉሱም በመንግሥቱ ሁሉ ላይ ይሾመው ዘንድ አሰበ፡፡ – ዳንኤል 6፡3
# #ዳንኤል በመጽሀፍ ቅዱሳችን ውስጥ ‹‹ መልካም መንፈስ›› ያለበት ገላጭ ያለው ሰው ነው፡፡ ምንም ዓይት ዋጋ ቢያስከፍለው እንኳን ለእግዚአብሔር ክብር በመስጠት የኖረ ነው፡፡ ዳንኤል እግዚአብሔርን የሚወድ እና በመሰጠቱም ሳይዋልል ያገለገለ ነው፡፡ ይህንን በማድረጉም እግዚአብሄር ከንጉሱ ጋር አቀረበው በምድሪቱ ባሉ በመሪዎች ሁሉ ላይ ሹመትን አገኘ፡፡ የዳንኤል መሰጠት በእግዚአብሔር የተፈተ ነበር፡፡
# #መሪዎች አንደ ዳንኤል ያሉ የንጉሱ ሞገስ ያላቸው ሰዎችን አይወዱም ፡፡ ከዚህም የተነሳ አንገላቱት ፤ ንጉሱም ማንኛውም ሰው ለሰላሳ ቀናት ወደ አምላኩ እንዳይጸልይ የሚከለክል ትዕዛዝ እንዲፈረም አስደረጉ፡፡ የንጉስን ትዕዛዝ መተላለፍ ወደ አናብስት ጉድጓድ የሚያስጥል ወንጀል ሆነ፡፡
# #ዳንኤል ከንጉስ ትዕዛዝ ይልቅ ለእግዚብሔር መሰጠት ዋነኛ ትኩረቱ ነበር፡፡ ታሪኩን የምታውቁት ከሆነ በታሪኩ ውስጥ እግዚአብሔር በስተመጨረሻ እንዴት እንዳከበረው እና እንደጠበቀው ታያላችሁ፡፡
# #በዚህ ዓይነት መልካም መንፈስ እንድትኖሩ አበረታታችኋለሁ፡፡ በሕይወታችሁ ሁሉ ለእግዚአብሔር ቆራጦች ሁኑ፡፡ ይህን ስታደርጉ በሕይወት ያላችሁን እውነተኛ ዐላም ከግብ ታደርሳለችሁም ፤ እግዚአብሔርንም በነገር ሁሉ እንደ ዳንኤል ታከብራላችሁ፡፡
09/06/2026
# #
#መግቢያ 1. የትምህርቱ አስፈላጊነት ትምህርቱ ለምን አስፈላጊ ሲባል መንፈሳዊ ሕፃንነት በተለይም የአገልግሎት ምንነትና ትርጉም በትክክል ያለማወቅ፤አውቆም በትክክል ያለመኖር ችግር ጎልቶ እየታየ ስላለ በአገልግሎት ምንነት ዙሪያ በተወሰነ መልክ ግንዛቤ ለመስጠት ነው። 1 ኛቆሮንቶስ 3 ፥ 1“ እኔም፥ወንድሞች ሆይ፥የሥጋ እንደመሆናችሁ፥በክርስቶስም ሕፃናት እንደመሆናችሁ እንጂ መንፈሳውያን እንደመሆናችሁ ” ልናገራችሁ አልቻልሁም። ዕብራውያን 5 ፥ 12-14" ከጊዜው የተነሳ አስተማሪዎች ልትሆኑ ሲገባችሁ፥አንድ ሰው ስለእግዚአብሔር ቃላት መጀመሪያ ያለውን የሕፃንነትን ትምህርት እንዲያስተምራችሁ እንደገና ያስፈልጋችኋልና፤የሚያስፈልጋችሁም ወተት ነው እንጂ ጠንካራ ምግብ አይደለም።ወተትየሚጋት ሁሉ ሕፃን ስለሆነ የጽድቅን ቃል አያውቅምና፤ጠንካራ ምግብ ግን መልካሙንና ክፉውን ለመለየት በስራቸው የለመደ ልቡና ላላቸው ለፍጹማን ሰዎች ነው። 2. የትምህርቱ ዓላማ የትምህርቱ ዓላማ፦እያንዳንዱን አገልጋይ ከመንፈሳዊ ሕፃንነትን በማላቀቅ ወደ መንፈሳዊ ብስለት ማሸጋገርና የአገልግሎትን ትክክለኛ ምንነትና ትርጉም በሚገባ እንዲረዱ ማድረግ ነው። 3. የትምህርቱ ግብ የትምህርቱ ግብ፦እያንዳንዱ አገልጋይ ከመንፈሳዊ ሕፃንነት ተላቆ የአገልግሎትን ትክክለኛ ምንነትና ትርጉም በሚገባ ተረድቶ እውነተኛ አገልጋይ ሆኖ ሲገኝ ማየት ነው። 1 # #የአገልግሎትምንነት 2 ዜና 29 ፥ 11 “ ልጆቼሆይ፥በፊቱ ትቆሙና ታገለግሉት ዘንድ፥አገልጋዮቹም ትሆኑዘንድ፥ታጥኑለትም ዘንድ እግዚአብሔር ” መርጦአችኋልና ቸል አትበሉ
# #መንፈሳዊአገልግሎትከመንፈሳዊሕይወትአይበልጥም። አገልግሎትበሕይወትተጨምቀውየሚወጣውጁስነው። በሕይወታችንኢየሱስማሳየትቀዳሚአገልግሎትነው። ከአገልግሎትበፊትሰውነትንሕያውናቅዱስአድርጎማቅረብይቀድማል። አገልግሎትምንድነው ?
07/06/2026
03/06/2026
🔥🔥🔥
#
# እህቴ እባክህ ወንድሜ ጊዜ ስጠው ለመንፈስ ቅዱስ ይስራብህ ይስራብሽ🔥🔥🔥
# 😭😭
➣በዚህ ዘመን ሰዎች እጅግ በጣም የብዙ ነገሮች ራሀብተኛ ሆነዋል፤ ይሁን እንጂ ለሚረባና ዋጋ ለሚኖረው ነገር አይደለም፤ በዚች ምድር ላይ ልንራበውና ልንፈልገው የሚገባ አንድ ነገር አለ፤ እርሱም🔥🔥 # ፤🔥🔥 # መንፈስ ራሀብተኛ ከሆናቹ በእውነት ነው የምላቹ በምድር ላይ እንደ እናንተ እድለኛ ሰው የለም ምክንያቱም ነገ ላይ በተጠማቹት ልክ ብቻ ሳይሆን ከዛም በላይ በመንፈሱ ተሞልታቹ በአለም አደባባይ ለብዙ ነፍሳት መዳን ምክንያት ስለምቶኑ፤ ስለዚህ ይህንን መንፈስ ከማንም በላይ ፈልጉት፤ ድንገት ሳታውቁት አንድ ቀን አይታቹት ወደማታውቁት መንፈሳዊ ክብር ውስጥ ትገባላቹ።
🔥🔥🔥🔥🔥
01/06/2026
♻️ 👉ዝሙት ታላቅ ኃጥያት ነው... የኖህን ዘመን ጥፋት ያመጣው ዝሙት ነው
የወሲብ ፊልሞችን ማየት እራስን በራስ ማርከስ (ሴጋ) ወሲብ ነክ ወሬዎችን ማውራት እነዚህን የመሳሰሉ ኃጢያቶች አንድ እራሱን ክርስቲያን ነኝ ብሎ በሚጠራ ሰው ሊፈፀሙ የማይገቡ እጅግ አፀያፊ በደሎች ናቸው።
እነዚህን ኃጢያቶች ተናዘን በጊዜ ካልተውናቸው በስተቀር ያለምንም ጥርጥር በምድር የህሊና ሸክም በሰማይ ቤትም የዘላለም እሳት እንደሚጥሉን አያጠራጥርም።
እንደ አብዛኛው ኃጥያት ሁሉ የነዚህም የዝሙት ኃጥያት ጀርባ አጋንንቶች አሉ፣ እኛ እነዚህን ኃጢያቶች ስንፈፅም ብዙ የማናስተውለው ነገር እነዚህ ኃጥያቶች ለአጋንንት እንደ በር መሆናቸውና ለሌላም ለከፋ ኃጥያትና እስራት እራሳችንን እያስተላለፍን መሆኑን አንዘንጋ።
የክርስትና ሕይወታችንን ፣ ለወደፊት የትዳር ሕይወታችንን ፣ ለመውለድ፣ ለማህበራዊ ሕይወታችኝ ፣ በራስ መተማመናችን፣ ለራሳችን ያለንን ክብር፣ የማስታወስ ችሎታችንን ፣ የአዕምሮ ብቃት የአካል ጥንካሬ፣ የአጥንትና የወገብ ጤና ፣ ካገባን በኋላ የሚኖረን ፆታዊ ግንኙነት ፣ በሥራችን የመሳሰሉትን እግዚአብሔር አክብሮ የሰጠንን ፀጋ የሚያፈራርስ ትልቅ ኃጥያት ነው።
መፍትሄው ምንድነው?
1/ እግዚአብሔርን መፍራት ፣ ንስሃ መግባት፣ ለማቆም መወሰን መፀለይ ፣ የእግዚአብሔርን እርዳታ መለመን
2/ መፆምና መስገድ ፣ ፀበል መጠመቅ
3/ ሕይወታችንን በክርስትና ትምሕርቶች ማነፅ ፣ ቤተክርስቲያን መሄድ፣ ቅዳሴ ማስቀደስ፣ ጉባኤ መከታተል።
4/ ሰውነታችን እጅግ ክቡር የእግዚአብሔር ማደሪያ መሆኑን ማመን
5/ ወሲብ ነክ ነገሮችን መራቅ፣ አለማየት ፣ አለማውራት
6/ ሁልጊዜ ኃጢያት ከሰራን በኋላ የበደለኝነት ስሜት እንደሚሰማን ማስታወስ
7/ እራሳችንን ማክበር
8/ በሰው ፊት የማናደርገውን ነገር ሁሉ ብቻችንንም አለማድረግ፣ ለራሳችን መታመን
9/ በፍፁም እራሴን አላረክስም እኔ ክርስቲያን ነኝ፣ ክርስቲያን ከዚህም ለበለጠ መታገስ ይጠበቅበታል ይቺ ፈተና ምንድናት እያሉ መፅናት
10/እግዚአብሔር ሰውነታቸውን በቅድስና ለሚጠብቁ ሰዎች የሚሰጠውን ፀጋ ማሰብ
አምላካችን እግዚአብሔር ከዚህ አፀያፊ ክፉ ስራ ሁላችንም ይሰውረን።አሜን🙏
31/05/2026
#
# #1ኛ/ ጋብቻ ማለት ለብቻቸው ሲኖሩ የነበሩ ሁለት ሰዎች በፍቅር፣ በኃላፊነት፣ በመተማመን እና በኪዳን አንድ ሆነው የሚኖሩበት የተባረከ ተቋም ነው። ጋብቻ ሁለት አካላት በአንድ ላይ ተጠምደው ከ“እኔ” ወደ “እኛ” የሚሸጋገሩበት ሕይወት ነው። እዚህ ውስጥ ሰው ብቻውን ለራሱ እንደሚኖር አይቀጥልም፤ ከዚያ በኋላ ሌላውን ሰው በማሰብ፣ በማክበር እና ከራሱ ጋር እኩል በማየት መኖርን ይማራል።
# #2ኛ/ ጋብቻ ከአንድ ወደ ሁለት ብቻ የሚያሸጋግር አይደለም፤ ሕይወትን የሚያበዛ፣ ቤተሰብን የሚያስፋፋ፣ ከዚያም ትውልድ የሚቀጥልበት ቦታ ነው። ዛሬ አንድና ሁለት የሆኑ ሰዎች ነገ ሦስት፣ አራት፣ አምስት ሆነው በልጆች የተሞላ ቤተሰብ ሊፈጥሩ ይችላሉ። ስለዚህ ጋብቻ የፍቅር ማቆያ ብቻ ሳይሆን የሕይወት መቀጠያ መሠረት ነው።
# #3ኛ/ ጋብቻ የወላጆችን ቤት ትቶ አዲስ ቤት የሚመሠረትበት ቦታ ነው። እናትና አባት ተትተው ሌላ እናት እና አባት የሚፈጠሩበት ቦታ ማለትም ዛሬ ልጅ የነበሩ ሁለት ሰዎች ነገ ቤተሰብ መሪዎች ሆነው ሌሎችን የሚያሳድጉበት ደረጃ ነው። ይህ ከትናንቱ ሕይወት ወደ አዲስ ኃላፊነት መሸጋገር ነው።
# #4ኛ/ ጋብቻ ደግሞ ቀለል ያሉና ከባድ የሆኑ ግጭቶች የሚፈጠሩበት ቦታ ነው። ሁለት ሰዎች ከተለያዩ ቤተሰብ ባህሎች፣ ከተለያዩ አስተሳሰቦች፣ ከተለያዩ ልምዶች ስለሚመጡ ልዩነት መኖሩ የማይቀር ነው። ነገር ግን የጋብቻ ውበት ግጭት ባለመኖሩ አይደለም፤ ግጭትን በትዕግሥት፣ በውይይት፣ በይቅርታ እና በፍቅር መፍታት በመቻሉ ነው።
# #5ኛ/ ጋብቻ እይታና አመለካከት የሚሰፋበት ቦታ ነው። ብቻውን የነበረ ሰው ሁሉን ነገር ከራሱ አንጻር ብቻ ያይ ይሆናል፤ በጋብቻ ውስጥ ግን ሌላውን ሰው ማዳመጥ፣ ሌላውን አስተያየት መቀበል፣ በሌላ ሰው ዐይን ሕይወትን ማየት ይማራል። ይህም ሰውን በስብዕና ያሳድገዋል፣ በጥበብም ያበረታዋል።
# # 6ኛ/ ጋብቻ “ለእኔ” ብቻ የሚባልበት ሳይሆን “ለእኛ” የሚባልበት ቦታ ነው። በዚህ ሕይወት ውስጥ የኔ ዕቅድ፣ የኔ ፍላጎት፣ የኔ ምርጫ ብቻ አይሰራም፤ የእኛ ራዕይ፣ የእኛ ዕቅድ፣ የእኛ መንገድ ይሆናል። ሁለቱም አንዱ ለአንዱ ሲኖሩ ነው ጋብቻ ትርጉም የሚኖረው።
# # 7ኛ/ ጋብቻ “እማዬ አባዬ” ብለው የሚጠሩ ልጆች የሚኖሩበት ደረጃ የሚፈጠርበት ቦታ ነው። ማለትም ከልጅነት ወደ ወላጅነት የሚሸጋገሩበት መንገድ ነው። የዛሬ ባልና ሚስት የነገ እናትና አባት ሊሆኑ ይችላሉ፤ ስለዚህ ጋብቻ ትውልድን የሚያቆም አይደለም፣ ትውልድን የሚያስነሳ ተቋም ነው።
# #8ኛ/ ጋብቻ እንደፈለጉ መውጣትና መግባት ቀርቶ በሥርዓት የሚኖሩበት ቦታ ነው። ይህ ሕይወት ነፃነትን ሙሉ በሙሉ የሚነጥቅ አይደለም፤ ነፃነትን በኃላፊነት ማኖር የሚያስተምር ነው። ሰው የሚያደርገውን ሁሉ ለራሱ ብቻ አይወስንም፤ ለቤቱ፣ ለጋብቻው፣ ለባልደረባው በማሰብ ይመራል።
# #9ኛ/ ጋብቻ ራስን በራስ ብቻ የሚመሩበት ሳይሆን በራስ ላይ ሌላ ሰው ተጽእኖ የሚኖረው ቦታ ነው። ይህ ግፍ ወይም ጭቆና አይደለም፤ የእርስ በርስ መገዛት፣ መከባበር፣ መሰማማት ነው። አንዱ ለሌላው የሚያስብ፣ የሚጠነቀቅ፣ የሚጠብቅ ሲሆን ነው ጋብቻ የሚበረታው።
# #10ኛ/ ጋብቻ አምሽቶ እንደፈለጉ መግባት ሳይሆን ጊዜን የሚያከብሩበት ቦታ ነው። ባልደረባህ የት እንደሆንክ፣ መቼ እንደምትመለስ፣ ምን እንደምታደርግ እንዲያውቅ መፍቀድ የፍቅር ምልክት ነው። ስርዓት የሌለው ሕይወት ጥርጣሬን ያመጣል፤ ስርዓት ያለው ሕይወት ግን ሰላምን ያመጣል።
# #11ኛ/ ጋብቻ የሚያዙበት ብቻ ሳይሆን የሚታዘዙበት ቦታ ነው ማለትም አንዱ ሌላውን በፍቅር ለማገልገል ራሱን ዝቅ የሚያደርግበት ቦታ ነው። በጋብቻ ውስጥ ሁለቱም ተቀባዮች ብቻ አይደሉም፤ ሰጪዎችም ናቸው። ፍቅር መቀበል ብቻ ሳይሆን ራስን ለሌላው መስጠት ነው።
# #12ኛ/ ጋብቻ ስልጣን፣ ክብር፣ ማዕረግ ብዙ የማይሰራበት ቦታ ነው። ከቤት ውጪ ሰው ምንም ያህል ታላቅ ስም ቢኖረው፣ በቤቱ ውስጥ ግን የሚፈለገው ትሕትና፣ ፍቅር፣ መከባበር እና መስማማት ነው። “አንተ” ሲባል የማይቀየም፣ “እኔ ማን ነኝ ታውቃለህ?” ብሎ የማይታበይ ሰው ጋብቻን በደንብ ሊኖር ይችላል።
# በአጭሩ ሲታይ የፍቅር ቦታ ነው፤ በጥልቀት ሲታይ የኃላፊነት ቦታ ነው፤ በእውነት ሲገለጥ ደግሞ ሰውን ከልጅነት ወደ ሙሉ ሰውነት የሚያድግ ትምህርት ቤት ነው። ጋብቻ የሁለት ሰዎች መገናኘት ብቻ አይደለም፤ የሁለት ልቦች ስምምነት፣ የሁለት ሕይወቶች ትስስር፣ የሁለት ዕጣ ፈንታዎች አንድ መሆን ነው።
# መጣችሁ።
ይህ ተቋም ለእናንተ የፍቅር ማረፊያ፣ የሰላም መኖሪያ፣ የበረከት ምንጭ እና የትውልድ መሠረት ይሁንላችሁ።
17/05/2026
13 የዘላለም ሕይወት እንዳላችሁ ታውቁ ዘንድ በእግዚአብሔር ልጅ ስም ለምታምኑ ይህን ጽፌላችኋለሁ።
15/05/2026
የኢትዮጵያ ቃለ ሕይወት ቤተ ክርስቲያን የ100ኛ አመት ክብረ በዓል ዝግጅትን አስመልክቶ የቤተ ክርስቲያኒቱ አመራሮችን እና አገልጋዮች የተገኙበት ግብረሃይሎችን የማደራጀት መርሃግብር በኢትዮጵያ ቃለ ሕይወት ቤተ ክርስቲያን ዋና ጽሕፈት ቤት ተካሄደ።
በስፍራው የኢትዮጵያ ወንጌል አማኞች አብያተ ክርስቲያናት ካውንስል ጠቅላይ ጸሐፊ
መጋቢ ጌትነት ለማ (ዶ/ር) እንዲሁም የአዲስ አበባ የሃይማኖት ተቋማት ጉባኤ ዋና ጸሐፊ መጋቢ ታምራት አበጋዝ ተገኝተዋል።
የአዲስ አበባ የሃይማኖት ተቋማት ጉባኤ ዋና ጸሐፊ የሆኑት መጋቢ ታምራት አበጋዝ በበኩላቸው በሚደረገው ክብረ በዓል ላይ ሰፊ የሆነ እይታ እና ትኩረት ይፈልጋሉ ያሏቸውን ሀሳቦችን አጋርተዋል።
በቤተ ክርስቲያኒቱ ምክትል ዋና ጸሐፊ ወንድሙ አበበ (ዶ/ር) በተጀመረው ፕሮግራም ላይ የመክፈቻውን ጸሎት ያደረጉት ደግሞ ጋሽ ሽፈራው ወልደ ሚካሄል ነበሩ።
1ኛ ዩሃንስ መልዕክትን መነሻ በማድረግ “በብርሃን እንመላለስ” በሚል ርዕስ የእግዚአብሔርን ቃል በኢትዮጵያ ቃለ ሕይወት ቤተ ክርስቲያን የሚሽን መምሪያ ዳይሬክተር የሆኑት ቀለሜ ቃና (ዶ/ር) አካፍለዋል ።
ከዚህ በመቀጠል የኢትዮጵያ ቃለ ሕይወት ቤተ ክርስቲያን ዋና ጸሐፊ ስምዖን ሙላት (ዶ/ር) በስፍራው ለተገኙት የቀድሞ የቤተ ክርስቲያኒቱ አመራሮች እና አገልጋዮች የእንኳን ደህና መጣችሁ መልዕክት አስተላልፈዋል።
የ100ኛ አመት ክብረ በዓል የክርስቶስን መምጫ የምንናፍቅበት መሆን ይጠበቅበታል ያሉት ደግሞ የቤተ ክርስቲያኒቱ ፕሬዝደንት ስሞኦን ሄሊሶ (ዶ/ር) ናቸው።
የዛሬው ቀን የኢትዮጵያ ቃለ ሕይወት ቤተ ክርስቲያን ተሃድሶ የሚጀመርበት ቀን ነው በማለት የተናገሩት የቤተ ክርስቲያኒቱ ምክትል ፕሬዝዳንት አቶ ዳንኤል ጫዕሜቦ በክብረ በዓሉ ላይ ቤተ ክርስቲያኒቱ ያነገበችውን ራዕይ አስታውቀው የተቋቋሙትን ግብረ ሃይሎች አስተዋውቀዋል።
ከዚህም በመቀጠል በቤተ ክርስቲያኒቱ ፕሬዚደንት እና ዋና ጸሐፊ መሪነት የምክክር ጊዜ ተካሂዷል።
Click here to claim your Sponsored Listing.
Category
Website
Address
Addis Ababa