Gebeyanu
የ ኢንተርኔት መገበያያ
02/04/2026
ዋልያ የሐሳብ እና መጻሕፍት መድረክ
ዋልያ መጻሕፍት ሴቶች በሀገር ግንባታ ተሳትፎ ስላላቸው
ኃላፊነት፣ ወሳኔ ሰጭነት እና መሪነት ዙሪያ
እንድንወያይ ፕሮግራም አሰናድትናል ።
በዕለቱ በተለያየ የሥልጣን እርከን ውስጥ የቆዩ እንዲሁም አሁንም በማገልገል ላይ የሚገኙ ባለ ብርቱ ሐሳብ የሆኑ እንስት ባለሙያዎችን የምንጋብዝ ይሆናል።
ሴቶች እና ኃላፊነት በሚል ርዕስ ዙሪያ
የየራሳቸውን የሕይወት ተሞክሮ እና ፍልስፍና የሚያቀርቡልን ተጋባዦች :
አምባሳደር ታደለች ኃይለሚካኤል
👉 ከሕይወት ልምድ ተሞክሮ
ሲሀም ካሚል
👉 የከተማና የኪነ-ሕንጻ ቅርሶች ተመራማሪ
ከከተሜነት እና የሴቶች ሥልጣን
መስከረም አዳነ
👉 ከፍልስፍና እና ሥርዓተ ጾታ ሙያ አንጻር
ቦታ፦ 4ኪሎ ኢክላስ ሕንጻ ዋልያ መጻሕፍት አዳራሽ
ቀን እና ሰዓት፦ መጋቢት 26 ቀን 2018 ዓ.ም ከሰዓት 8:00 ጀምሮ
ዋልያ መጻሕፍት
24/10/2025
"የመሀላ ጉልበት" ✋✋
ቅዳሜ ከሰዓትዎን "የመሀላ ጉልበት"✋✋ በሚል ርእስ አውታር ቃሎቻችንን የማያ እና የመወያያ መድረክ አዘጋጅተናል። ባዘጋጀነው ልዩ የፓነል ውይይት ከእኛ ጋር ያሳልፉ! ለውይይቱ መነሻ ሀሳብ እና ትንተና እንዲያቀርቡልን በህግ፣ በሥነ ጽሑፍ፣ በፍልስፍና ጠልቀው የተመለከቱ በየ ዘርፉ ያሉ ምሁራንን ጋብዘናል።
ከህግ አቶ ታምሩ ወንድምአገኝ የህግ አማካሪ እና ጠበቃ፣ እንዲሁም አቶ ቢኒያም አህመድ የህግ እና ቢዝነስ መምህር እና ተመራማሪ
ከስነ-ፅሁፍ ጥላሁን ተሊላ /ዶክተር /
ከፍልስፍና ሀኒባል በቀለ /እጩ ዶክተር/
አወያይ
ዮናስ ታረቀኝ
ኑ እና ሐሳብ ተካፈሉ፤ ሐሳብ አካፍሉ!
ቦታ: 4ኪሎ ኢክላስ ህንፃ ዋልያ መፃሕፍት አዳራሽ
ቀን እና ሰዓት : ቅዳሜ ጥቅምት 15 ቀን 2018 ዓም ከሰዓት 8:00 ጀምሮ
29/07/2025
የፍሎረንስ አሰበ ትርጉም የልጆች መፅሐፍ በቅርብ ቀን...
29/07/2025
የ ደራሲ ጎበና ዳንኤል (ሠርቅ.ዳ) ተውዳጅ ስራ የሆነው #ቆንጆዎቹ በቅርብ ቀን በገበያ ይውላል
13/07/2025
09/07/2025
06/02/2025
ከነገ ጥር 30 2017 ዓ.ም ጀምሮ በሁሉም አዲስ አበባ ውስጥ ባሉ መፅሐፍ ቤቶች ያገኙታል
13/04/2024
ጋሽ አለማየሁ ገልጋይ እንኳን ተወለድክ እያልን
1. በዓለማየሁ ገላጋይ :
#ማዕበል ጠሪ ወፍ
2. ስለ ዓለማየሁ ገላጋይ:
#መልከዓ-አለማየሁ
እንዲሁም በድጋሜ ለ3ኛ ህትመት
የበቃውን ቤባንያን እያነበብን "ዓለማችንን" እንድናይ ዋልያ መፅሃፍ ይጋብዛል።
Click here to claim your Sponsored Listing.
Category
Contact the business
Telephone
Website
Address
Addis Ababa
Opening Hours
| Monday | 09:00 - 17:00 |
| Tuesday | 09:00 - 17:00 |
| Wednesday | 09:00 - 17:00 |
| Thursday | 09:00 - 17:00 |
| Friday | 09:00 - 17:00 |
| Saturday | 09:00 - 12:00 |