Fikiru Kumera
Contact information, map and directions, contact form, opening hours, services, ratings, photos, videos and announcements from Fikiru Kumera, Health/Beauty, Addis ababa, Ababa.
06/04/2024
ለውጡ የተጀመረበትን 6ኛ ዓመት ለማሰብ እና የተገኙ ውጤቶችን ለማስቀጠል ያለመ የድጋፍ ሰልፍ በአዲስ አበባ እየተካሄደ ነው
ለውጡ የተጀመረበትን 6ኛ ዓመት ለማሰብ እና የተገኙ ውጤቶችን ለማስቀጠል ያለመ የድጋፍ ሰልፍ ከማለዳው 12 ሰዓት ጀምሮ “ለሀገራችን ብልፅግና በኅብረት እንቆማለን!” በሚል መሪ ቃል በአዲስ አበባ እየተካሄደ ይገኛል።
በድጋፍ ሰልፉ ላይ በርካታ የመዲናዋ እና የአጎራባች አካባቢዎች ነዋሪዎች ተገኝተዋል።
ሰልፈኞቹ ለውጡን እና የለውጡን አመራር የሚደግፉ የተለያዩ መፈክሮችን እያሰሙ ይገኛሉ።
ከመፈክሮቹ መካከል፣ ድሎችን በማዝለቅ እና ጉደለቶችን በማረም ለውጡን እናስቀጥላለን!” “ለሀገራችን ብልፅግና በኅብረት እንቆማለን!”፣ “መንግሥት አዲስ አበባን ለነዋሪዎቿ ምቹ እና ማራኪ ከተማ ለማድረግ የሚሠራውን ሥራ ከልብ እንደግፋለን!” የሚሉ ይገኙበታል።
እንዲሁም፣ “አዲስ አበባችን በመሪዎቿ እና በሕዝቡ ትብብር ወደ ተሟላ ብልፅግና የምትሸ ጋገርበት ጊዜ አጭር ነው!” “የፅንፈኝነት እና የአክራሪነት አስተሳሰብ እና ተግባርን በፅናት እንታገላለን!” “ጠንካራ ኢትዮጵያ በኅብረ ብሔራዊ ወንድማማችነት ላይ ትገነባለች!” የሚሉ መፈክሮችንም እያሰሙ ነው።
02/04/2024
በዛሬው ዕለት 60 ሺሕ የመኖሪያ ቤቶች ግንባታ በሚጀመርበት አካባቢ ያሉ የአቃቂ ቃሊቲ ነዋሪዎች ለውጡ የተጀመረበትን መጋቢት 24 ቀንን በማስመልከት ደስታቸውን ገልጸዋል::
21/03/2024
የመከላከያ ዋር ኮሌጅ ያሰለጠናቸውን ጀነራል መኮንኖችና ከፍተኛ መኮንኖች አስመረቀ
*****************
(ኢ ፕ ድ)
የኢፌዴሪ መከላከያ ዋር ኮሌጅ በመደበኛ አጭር የትምህርት መርሐግብሮች ያሰለጠናቸውን ጀነራል መኮንኖችና ከፍተኛ መኮንኖች አስመረቀ።
የመከላከያ ዋር ኮሌጅ ዋና አዛዥ ብርጋዴር ጄኔራል ቡልቲ ታደሰ፤ ኮሌጁ በመደበኛ አጭር ኮርስ ስልጠና ጄነራል መኮንኖች እና ከፍተኛ መኮንኖችን አሰልጥኖ በዛሬው እለት አስመርቋል።
በዛሬው ዕለት የተከናወነው ጄነራል መኮንኖችና ከፍተኛ መኮንኖች ምረቃም ኮሌጁ ተልዕኮውን በብቃት እየተወጣ ለመሆኑ ማሳያ ነው ብለዋል፡፡
ተመራቂዎች በቆይታቸው ባገኙት ዕውቀት ሌሎች መኮንኖችን ለማፍራት መትጋትና የዕለት ተዕለት ስራዎቻቸውን በብቃት መወጣት እንዳለባቸው አሳስበዋል፡፡
በምረቃ ሥነ ስርዓቱ የጦር ኃይሎች ጠቅላይ ኢታማዦር ሹም ፊልድ ማርሻል ብርሃኑ ጁላ፣ የውጭ ጉዳይ ሚኒስትር ዴኤታ አምባሳደር ብርቱካን አያኖ፣ በውጭ ጉዳይ ሚኒስቴር የአፍሪካ ጉዳዮች ዳይሬክተር ጀኔራል አምባሳደር ፍስሃ ሻውል እና በሕዝብ ተወካዮች ምክር ቤት የውጭ ግንኙነትና የሰላም ጉዳዮች ቋሚ ኮሚቴ ሰብሳቢ ዶክተር ዲማ ነገዎ ተገኝተዋል።
መጋቢት 12 ቀን 2016 ዓ.ም
21/03/2024
ቃልን በተግባር ለኢትዮጵያ ብልጽግና!
ፓርቲው የመደመር ዕሳቤን መሰረት አድርጎ የኢትዮጵያዊያንን የተጋመደና የተሰናሰነ ማንነት በህብረብሔራዊነት በማጽናት የበለፀገችና የግዛት አንድነቷ የተከበረ ሀገርን ለመገንባት በፅናት እየሰራ ይገኛል
አቶ መገርሳ ገላና
የየካ ክፍለ ከተማ ብልፅግና ፓርቲ ቅርንጫፍ ጽ/ቤት ሃላፊ
በኮንፈረንሱ ማጠቃለያ የፓርቲዉ የግማሽ ምርጫ ዘመን አፈፃፀም እና የቀሪ ምርጫ ዘመን የትኩረት አቅጣጫ ሰነድ ያቀረቡት የየካ ክፍለ ከተማ ብልፅግና ፓርቲ ቅርንጫፍ ፅህፈት ቤት ኃላፊ አቶ መገርሳ ገላና ፓርቲው ባለፉት አመታት ያከናወናቸውን የልማት ፣ የመልካም አስተዳደር ፣ ማህበራዊ ጉዳዮች እንዲሁም ህብረ-ብሔራዊነትን ለማጠናከር የተሰሩ ስራዎችን ያቀረቡ ሲሆን ባለፉት 5 የለውጥ ዓመታት ፓርቲያችን ብልፅግና ታላላቅ ፕሮጀክቶችን ጀምሮ መጨረስን ያስተማረና ፕሮጀክቶችን ጀምሮ በአጭር ጊዜ በማጠናቀቅ ለህዝቦች ጥቅም ለማዋል እየተጋ ይገኛል ብለዋል።
21/03/2024
"ብልፅግና ፓርቲ ለህዝብ የገባውን ቃል በመጠበቅ ለሁሉም የምትመች ሀገር እየገነባ ነው"
አቶ ብርሀኑ ረታ
የየካ ክፍለ ከተማ ዋና ስራ አስፈፃሚ
መጋቢት 12/2016 ዓ.ም የካ ወረዳ 07 ኮሙኒኬሽን
የየካ ክፍለ ከተማ ብልፅግና ፓርቲ ቅርንጫፍ ፅህፈት ቤት "ቃልን በተግባር ለኢትዮጵያ ብልፅግና" በሚል መሪ ቃል ከክፍለ ከተማው ብልፅግና ፓርቲ አባላት ጋር ሲያካሂድ የቆየውን ህዝባዊ ኮንፈረንስ የማጠቃለያ መርሀ ግብር በማካሄድ ላይ ነው።
19/03/2024
18/03/2024
ፓርቲያችን ብልጽግና መሰረቱ ሰው በመሆኑም ለህዝብ የገባውን ቃል የሚያከብር የሚፈጽምም ነው። በዚህም በርካታ ሰውተኮር ተግባራትን በስኬት በመፈጸም የማህበረሰቡን ቀጥተኛ ተጠቃሚነት እያረጋገጠ ይገኛል። ፓርቲያችን እያስመዘገባቸው የሚገኙትን ፖለቲካዊ፣ ኢኮኖሚያዊና ማህበራዊ ድሎች አጠናክሮ በማስቀጠል በቀጣይ የምርጫ ጊዜ ለህዝብ የገባቸውን ተግባራት በቁርጠኝነት ለመተግበር ከመላው አባላቱና ደጋፊዎቹ ጋር ውይይት እያደረገ ይገኛል።
በየካ ክ/ከተማ ብልፅግና ፓርቲ በሁሉም ወረዳዎች በሁሉም መሰረታዊ ፓርቲ አመራሮች ሲካሄድ የነበረው የመሰረታዊ ፓርቲ ኮንፈረንስ ሂደት ከወረዳ አስተባባሪዎች ጋር ተገምግሟል።
በግምገማ መድረኩም የክ/ከተማው የብልፅግና ፓርቲ ጽ/ቤት ሃላፊ አቶ መገርሳ ገላና እንደገለፁትበፓርቲያችን መተዳደሪያ ደንብ ላይ በተቀመጠው መሰረት የተካሄደው የአባላት ኮንፈረንስ በመሰረታዊ ድርጅት በድምቀት እንደተካሄደ ገልፀው በቀጣይ በወረዳ ደረጃ ለሚካሄደው መድረክ ቅድመ ዝግጅት ተጠናክሮ መቀጠል እንደሚገባ አቅጣጫ አስቀምጠዋል።
እየተደረገ ባለው የመላው አባላችን ኮንፈረንስ ላይ የተጀመሩ የልማት ኢንሸቲቮችን በማጠናከር በተለይም በሌማት ትሩፋት፣ በአረንጓዴ አሻራ፣ በበጋ ስንዴና እንሰሳት እርባታ ስራዎችን እናስቀጥላለን። የፓርቲያችንን ህዝባዊ ቅቡልነት በማጽናት ጉድለቶችን እያረምን ቀሪ ተግባራት በትኩረት በመፈጸም የስራ ዕድልና የልማት ስራዎችን በማስቀጠል በብሔራዊ ገዥ ትርክት አንድነታችንን እያፀናን ህብረብሔራዊ የመደመር ጉዟችን እንደሚቀጥል ማረጋገጥ ተችሏል።
በአጠቃላይ በከተማችን ብሎም በየካ ክ/ከተማ ሁሉም ወረዳዎች እየተካሄደ በሚገኘው የብልጽግና ፓርቲ አባላት ኮንፈረስ ፓርቲያችን የጀመረው የሁለንተናዊ የብልጽግና ጉዞ በማስቀጠል ህዝብ የሰጠውን አደራ በብቃት ለመፈጸም ቃልን ማደስ የተቻለበት አውድ ተፈጥሯል። የህዝብን ድምጽ በማክበር የመልካም አስተዳደር ጥያቄዎችን በመፍተታና ቀልጣፋ አገልግሎት በመስጠት የጽንፈኝነት አስተሳሰብን በመታገል የሰላም ዕሴቶቻችንን ጠብቀን ከነጠላ ዕውነት ወደወል ዕውነት በመሻገር ብሔራዊ ገዥ ትርክትን በመትከል ሀብቶቻችንን በአግባቡ በመጠቀምና በማስተዳደር ከዕዳ ወደምንዳ የሚደረገውን ብልጽግናዊ ጉዞ ለመፈጸም ቃልን ያደሰበት ሆኗል።
14/03/2024
ለከተማችን ትልቅ የምስራች እነሆ!
በ100 ሺሕ ካሬ ሜትር ስፍራ ላይ ያረፈው የሴቶች የተሀድሶና የክህሎት ማበልጸጊያ ማዕከል ለአገልግሎት ክፍት ይደረጋል።
ማዕከሉ በዋነኛነት በሴተኛ-አዳሪነት ላይ የተሰማሩ ሴቶችን በመቀበል ሙያዊ እና ስነ ልቦናዊ ድጋፍ፣ ክትትልና ስልጠናዎችን እንዲያገኙ በማድረግ ወደ ስራ እንዲሰማሩ የሚያደርግ ሲሆን፣ በአንድ ዙር ብቻ 10,000 ሴቶችን ተቀብሎ የማሰልጠን አቅም አለው።
ወጣት ሴቶቹ በማዕከሉ ቆይታቸው ከሚያገኙት የስነ ልቦና ድጋፍ በተጨማሪ በስነ-ውበት፣ በከተማ ግብርና ፣ በምግብ ዝግጅት፣ በከተማ ውበት አጠባበቅ፣ በኮምፒዩተር ሙያ፣ በሞግዚትነት፣ በመስተንግዶ፣ በፀጉር ስራ፣ በኤሌክትሪክና ሸክላ ስራ፣ በእንጨት ስራዎች፣ በልብስ ስፌት እንዲሁም በሌሎች የሙያ ዘርፎች በቂ ስልጠና በመስጠት ወደ ስራ እንዲገቡ የምናደርግ ይሆናል።
ከዚህም በተጨማሪ ማዕከሉ ምቹ የመኝታ ክፍሎች፣ ቤተ-መጻህፍት፣ የቤት ውስጥ ስፖርት ማዘውተሪያ ጂምናዚየም፣ ምቹ የመመገቢያ አዳራሾች፣ ዘመናዊ የምግብ ማብሰያ፣ በመጀመሪያ ደረጃ ሆስፒታል አቅም የተደራጀ ዘመናዊ የህክምና ማዕከል፣ የተግባራዊ ልምምድና የሰርቶ ማሳያ ማዕከላት፣ የልብስ ንጽህና መጠበቂያ ላውንደሪዎች፣ የህጻናት ማቆያና እንክብካቤ ማዕከላት፣ የህጻናት ስነ-አዕምሮአዊ እድገት ክትትልና ልህቀት ክፍል እንዲሁም የስፖርት ማዘውተሪያ ሜዳዎች የተካተቱበት ግዙፍ ፕሮጀክት ነው።
ማህበራዊ ፍትህ የነገሰባት ከተማን ለመገንባት ለህዝባችን የገባነውን ቃል እየፈጸምን አሁንም የመረጠንን ህዝብ በታማኝነትና በትጋት ማገልገላችንን አጠናክረን እንቀጥላለን!
ፈጣሪ ኢትዮጵያን እና ህዝቦቿን ይባርክ!
Magaalaa keenyaaf misiraachoo guddaan kunoo!
Giddugalli haaromsaa fi dandeettii dagaagsuu dubartootaa lafa kaaree meetira kuma 100 qabate tajaajilaaf banaa ni taasifama.
Giddugalichi irra caalaa dubartoota daldaala saal-qunnamtii irratti bobba'an simachuun hordoffii fi leenjii deeggarsa ogummaa fi qor-qalbii akka argatan taasisuun gara hojiitti akka bobba'an kan taasisu yoo ta'u, marsaa tokko qofaatti dubartoota 10,000 simachuun dandeettii leenjisuu qaba.
Dubartoonni dargaggoonni turtii isaaniitiin deeggarsa qor-qalbii argatan cinaatti miidhaginaan, qonna magaalaan, qophii nyaataan, eegumsa miidhagina magaalaan, ogummaa kompiitaraan, kununsa daa’immanii, keessummeessuun, hojii mana rifeensaan, hojii elektirikaa fi supheen, hojii mukaan, hodhaa huccuu akkasumas dameewwan hojii biroon leenjii gahaa kennuun gara hojiitti akka bobba’an kan taasisu ta'a.
Kanatti dabalees giddugalichi kutaa ciisichaa mijataa, mana kitaabaa, jiiminaaziyeemii hojii ispoortii mana keessaa, galma soorataa mijataa, bilcheessa nyaataa ammayyaa, giddugala yaalaa ammayyaa dand
13/03/2024
የዓለም ባንክ ዋና ዳይሬክተር በኢትዮጵያ የወጣቶች የስራ ላይ ልምምድና የልማታዊ ሴፍትኔት ፕሮግራም ፕሮጀክቶችን ጎበኙ፡፡
የዓለም ባንክ ዋና ዳይሬክተር ሚስተርስ ፍሎሪ ቤርፕ ንጋሩኮ በዓለም ባንክ የሚደገፈውን የወጣቶች የስራ ላይ ልምምድና የዘላቂ ኑሮ ማሻሻያ የከተማ ልማታዊ ሴፍትኔት ፕሮግራሞች ያሉበትን ደረጃ ተዘዋውረው በመመልከት ይፋዊ ጉብኝት አድርገዋል፡፡
በጉብኝት መርሃ ግብሩ ላይ የከተማ ልማትና ኮንስትራክሽን ሚኒስተር ሚኒስትር ወ/ሮ ጫልቱ ሳኒ ፣በበአዲስ አበባ ከተማ አስተዳደር በምክትል ከንቲባ ማዕረግ የስራና ክህሎት ቢሮ ሀላፊ አቶ ጥራቱ በየነ ፣ የለሚ ኩራ ክ/ከተማ ዋና ስራ አስፈጻሚ አቶ ታረቀኝ ገመቹን ጨምሮ በርከታ ባለስልጣናት የተሳተፉ ሲሆን
ለወጣቶች የስራ ላይ ልምምድ በመሰልጠን ላይ ያሉ ወጣቶችን ፣ በወረዳ 14 አስተዳደር በሚገኘው ህዳሴ ጤና ጣቢያ ውስጥ በልማታዊ ሴፍትኔት ተጠቃሚዎች የተሰራውን የከተማ ግብርና ስራ ተመልክተዋል።
የክ/ከተማው ዋና ስራ አስፈጻሚ አቶ ታረቀኝ ገመቹ እንግዶችን ተቀብለው የእንኳን ደህና መጣችሁ ንግግር ያደረጉ ሲሆን በምክትል ከንቲባ ማዕረግ የስራና ክህሎት ቢሮ ሀላፊ አቶ ጥራቱ በየነ በከተማ አቀፍ ደረጃ እየተሰሩ ባሉ ተግባራት ላይ ሰፋ ያለ ማብራሪያ ሰጥተዋል፡፡
በመጨረሻም የዓለም ባንክ ዋና ዳይሬክተር ሚስተርስ ፍሎርቤርፕ ንጋሩኮ በኢትዮጵያ የዓለም ባንክ የወጣቶች የስራ ላይ ልምምድና የዘላቂ ኑሮ ማሻሻያ የከተማ ልማታዊ ሴፍትኔት እየተከናወነበት ያለው አግባብ በእጅጉ የሚበረታታ መሆኑንና ኢትዮጵያም ተግባሩን ተቀብላ በርካታ ስራ እየሰራች መሆኑን ጠቁመው ፕሮግራሙን ለማጠናከር ለሚቀርብ ማንኛውም ጥያቄ አስፈላጊውን ድጋፍ እንደሚያደርጉም ቃል ገብተዋል፡፡
ለሚ ኩራ ኮሚዩኒኬሽን
መጋቢት 04/2016 ዓ.ም
05/03/2024
ጠቅላይ ሚኒስትር ዐቢይ አሕመድ በተገኙበት የሚኒስትሮች ምክር ቤት የ2016 የሁለተኛው ሩብ አመት የስራ አፈፃፀም መገምገም ጀምሯል። ግምገማው አራቱን የአስተዳደርና ፍትህ፣ የማኅበራዊ፣ የኢኮኖሚያዊ ዘርፎችን በተመለከተ በቀረቡ አፈፃፀሞች ላይ በማተኮር ተጀመሯል። ጠቅላይ ሚኒስትር ዐቢይ አሕመድ መሰል የግምገማ መድረኮች በመንግሥት ተቋማት የመፈፀም ባህልን ለማዳበር የጀመሯቸው መሆናቸው ይታወሳል።
05/03/2024
በዓድዋ ድል መታሰቢያ እና አራዳ ህንጻ መሃል ያለው እንደ አዲስ የተገነባው መንገድ ከዛሬ ጀምሮ ለትራፊክ ክፍት
ስለተደረገ አሽከርካሪዎች መንገዱን መጠቀም እንደምትችሉ እናሳውቃለን::
Click here to claim your Sponsored Listing.
Category
Contact the business
Telephone
Address
Ababa